መጽሐፈ ሲራክ 34
34
1በጎ ልቡናንና የሚጣፍጥ እህልን አይንቁትም፤
ለባለጸግነት መትጋት ፈጽሞ ሰውነትን ያከሳል፥
ገንዘብንም ማሰብ እንቅልፍን ያሳጣል።
2የሚጠራጠሩትን ማሰብ በእንጉልቻ እንቅልፍን ያስረሳል፤
ከባድ ሕማምም ያተጋል፥ እንቅልፍንም ያሳጣል።
3ባለጸጋ ገንዘብ ያደልብ ዘንድ ይዞራል፤
ባረፈም ጊዜ በጥጋብ ደስ ይለዋል።
4ድሃ ገንዘብ በማጣት ይደክማል፤
ባረፈም ጊዜ ወደ ልመና ይመለሳል።
5ገንዘብን የሚወድ ሰው አይጸድቅም፤
ኀጢአትንም የሚወዳት ሰው ይከተላታል።
6ስለ ገንዘብ የወደቁ ሰዎች ብዙ ናቸው፤
ሞታቸውንም በፊታቸው አዩኣት።
7ገንዘብ ለሚፈልጓት የእንቅፋት ዕንጨት ናት፤
ሰነፍ ሰው ሁሉ በእርስዋ ይሰነካከላል።
8ከኀጢአት ንጹሕ የሆነ፥
ልቡናውንም ከገንዘብ በኋላ ያላስከተለ ባለጸጋ ብፁዕ ነው።
9ለወገኖቹ መልካም ነገር የሚያደርግ ማንነው?
እንጃ! እርሱን እናደንቀዋለን።
10በእርሱ የተፈተነ፥ ያልሳተም
እርሱም መመኪያ የሆነው ማን ነው?
ኀጢአት መሥራት ሲቻለው ኀጢአት የማይሠራ ማን ነው? እንጃ።
ክፉ መሥራት ሲቻለውስ ክፉ የማያደርግ ሰው ማን ነው?
11በረከቱ ትጸናለች፤ ምጽዋቱም በአሕዛብ ሀገር ትሰማለች።
የማዕድ ሥርዐት
12በታላቅ ማዕድም ብትቀመጥ
ለመብላት ጉሮሮህን አትክፈት፤
ምግቡም ምን ያህል ነው ብለህ አታጋን፤
13የሰው ዐይን ክፉ እንደ ሆነ አስብ፤
ከሰው ዐይን የሚከፋ ምን አለ?
ስለዚህም ነገር ዐይን ታለቅሳለች።
14ላየኸው ሁሉ አትሳሳ፤
እጅህን አትንከር፤
ወጭቱን ወደ አንተ አትጎትት፥
ድስቱንም አትጥረግ።
15ባልንጀራህ የጋበዘህን ዕወቅ፤
ያቀረበልህንም ሁሉ ተረዳ።
16ያቀረቡልህን እንደ ብልህ ሰው ሁነህ ብላ፤
ባልንጀራህን እንዳታስጸይፍ ስታላምጥ ምላስህን አታጩህ።
17እንደ ብልህ ሰው ሁሉ አስቀድመህ ተው፤ አትሳሳ፤
እንደማይጠግብ ሰውም አትሁን።
18በብዙዎች መካከልም ብትቀመጥ
እጅህን አስቀድመህ አትስደድ።
19በመኝታህ ሆድህን እንዳይከብድህ፥
ጥቂት እንደሚበቃው እንደ ዐዋቂ ሰው መጥነህ ብላ።
20መጥኖ የሚመገብ ሰው እንቅልፉ ጤና ነው፤
ከእንቅልፉም በጧት በነቃ ጊዜ ሆዱን አይከብደውም፤
ለማይጠግብ ለስሱ ሰው በሽታው ቍንጣን፥ ጓታና ብስና ነው።
21ትበላ ዘንድ ግድ ቢሉህ ቀድመሃቸው ተነሥ፤
ከመብላትም ዕረፍ።
22ልጄ ሆይ አድምጠኝ፤ ምክሬንም አትናቅ፤
ኋላ ነገሬን ታገኘዋለህ፤
ምንም እንዳታጣ በምትሠራው ሥራ ሁሉ ደካማ አትሁን።
23ለጋስን ሰው በሥራው ማማር ይመርቁታል፤
የደግነቱ ምስክርነትም የታመነ ነው፤
ንፉግ ሰውንም በክፉ ሥራው ይረግሙታል።
የክፋቱ ምስክርነትም የተረዳ ነው።
24መጠጥ ብዙ ሰዎችን አስትዋቸዋልና፥
ወይን በጠጣህ ጊዜ አትታበይ።
25ጽኑ ብረትን በወናፍ ይፈትኑታል፤
እንዲሁም ሁሉ የትዕቢተኞችን ልቡና ወይን ይፈትነዋል።
26የሰው ሕይወቱ ወይን መጠጣት ነው፤
መጥኖ ለሚጠጣውም ሰው ደስታ ነው፤
እርሱ ለሰው ደስታ ሊሆን ተፈጥሯልና
ወይን ለማይጠጣ ሰው ሕይወቱ ምንድን ነው?
27ለልብ ደስታ ነው፤ ለሰውነትም ሐሤት ነው፤
ወይንን መጥኖ በጊዜው መጠጣት መልካም ነው።
28ወይን የልቡና ኀዘንን ያስረሳል፤
ለሚያለቅስና ለሚያዝን ሰውም ወይንን አጠጣው።
29ሰነፍ ሰው ወይን በጠጣ ጊዜ ክርክርን ያበዛል፥ ይስታል፥ ይበድላልም፤
የመጠጥ ብዛት ኀይልን አያስገኝም፤ ቍስልንም አያሳጣም።
30ወይን ጠጥቶ ሳለ ባልንጀራህን አትቈጣው፤
ልቡ ደስ ብሎት ሳለም አታሳዝነው፤
የምትነቅፈውንም አትንገረው፤
እርሱ ሰክሮ ሳለ ጉዳይህን አትለምነው፤ አትዘብዝበውም።
Currently Selected:
መጽሐፈ ሲራክ 34: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
መጽሐፈ ሲራክ 34
34
1በጎ ልቡናንና የሚጣፍጥ እህልን አይንቁትም፤
ለባለጸግነት መትጋት ፈጽሞ ሰውነትን ያከሳል፥
ገንዘብንም ማሰብ እንቅልፍን ያሳጣል።
2የሚጠራጠሩትን ማሰብ በእንጉልቻ እንቅልፍን ያስረሳል፤
ከባድ ሕማምም ያተጋል፥ እንቅልፍንም ያሳጣል።
3ባለጸጋ ገንዘብ ያደልብ ዘንድ ይዞራል፤
ባረፈም ጊዜ በጥጋብ ደስ ይለዋል።
4ድሃ ገንዘብ በማጣት ይደክማል፤
ባረፈም ጊዜ ወደ ልመና ይመለሳል።
5ገንዘብን የሚወድ ሰው አይጸድቅም፤
ኀጢአትንም የሚወዳት ሰው ይከተላታል።
6ስለ ገንዘብ የወደቁ ሰዎች ብዙ ናቸው፤
ሞታቸውንም በፊታቸው አዩኣት።
7ገንዘብ ለሚፈልጓት የእንቅፋት ዕንጨት ናት፤
ሰነፍ ሰው ሁሉ በእርስዋ ይሰነካከላል።
8ከኀጢአት ንጹሕ የሆነ፥
ልቡናውንም ከገንዘብ በኋላ ያላስከተለ ባለጸጋ ብፁዕ ነው።
9ለወገኖቹ መልካም ነገር የሚያደርግ ማንነው?
እንጃ! እርሱን እናደንቀዋለን።
10በእርሱ የተፈተነ፥ ያልሳተም
እርሱም መመኪያ የሆነው ማን ነው?
ኀጢአት መሥራት ሲቻለው ኀጢአት የማይሠራ ማን ነው? እንጃ።
ክፉ መሥራት ሲቻለውስ ክፉ የማያደርግ ሰው ማን ነው?
11በረከቱ ትጸናለች፤ ምጽዋቱም በአሕዛብ ሀገር ትሰማለች።
የማዕድ ሥርዐት
12በታላቅ ማዕድም ብትቀመጥ
ለመብላት ጉሮሮህን አትክፈት፤
ምግቡም ምን ያህል ነው ብለህ አታጋን፤
13የሰው ዐይን ክፉ እንደ ሆነ አስብ፤
ከሰው ዐይን የሚከፋ ምን አለ?
ስለዚህም ነገር ዐይን ታለቅሳለች።
14ላየኸው ሁሉ አትሳሳ፤
እጅህን አትንከር፤
ወጭቱን ወደ አንተ አትጎትት፥
ድስቱንም አትጥረግ።
15ባልንጀራህ የጋበዘህን ዕወቅ፤
ያቀረበልህንም ሁሉ ተረዳ።
16ያቀረቡልህን እንደ ብልህ ሰው ሁነህ ብላ፤
ባልንጀራህን እንዳታስጸይፍ ስታላምጥ ምላስህን አታጩህ።
17እንደ ብልህ ሰው ሁሉ አስቀድመህ ተው፤ አትሳሳ፤
እንደማይጠግብ ሰውም አትሁን።
18በብዙዎች መካከልም ብትቀመጥ
እጅህን አስቀድመህ አትስደድ።
19በመኝታህ ሆድህን እንዳይከብድህ፥
ጥቂት እንደሚበቃው እንደ ዐዋቂ ሰው መጥነህ ብላ።
20መጥኖ የሚመገብ ሰው እንቅልፉ ጤና ነው፤
ከእንቅልፉም በጧት በነቃ ጊዜ ሆዱን አይከብደውም፤
ለማይጠግብ ለስሱ ሰው በሽታው ቍንጣን፥ ጓታና ብስና ነው።
21ትበላ ዘንድ ግድ ቢሉህ ቀድመሃቸው ተነሥ፤
ከመብላትም ዕረፍ።
22ልጄ ሆይ አድምጠኝ፤ ምክሬንም አትናቅ፤
ኋላ ነገሬን ታገኘዋለህ፤
ምንም እንዳታጣ በምትሠራው ሥራ ሁሉ ደካማ አትሁን።
23ለጋስን ሰው በሥራው ማማር ይመርቁታል፤
የደግነቱ ምስክርነትም የታመነ ነው፤
ንፉግ ሰውንም በክፉ ሥራው ይረግሙታል።
የክፋቱ ምስክርነትም የተረዳ ነው።
24መጠጥ ብዙ ሰዎችን አስትዋቸዋልና፥
ወይን በጠጣህ ጊዜ አትታበይ።
25ጽኑ ብረትን በወናፍ ይፈትኑታል፤
እንዲሁም ሁሉ የትዕቢተኞችን ልቡና ወይን ይፈትነዋል።
26የሰው ሕይወቱ ወይን መጠጣት ነው፤
መጥኖ ለሚጠጣውም ሰው ደስታ ነው፤
እርሱ ለሰው ደስታ ሊሆን ተፈጥሯልና
ወይን ለማይጠጣ ሰው ሕይወቱ ምንድን ነው?
27ለልብ ደስታ ነው፤ ለሰውነትም ሐሤት ነው፤
ወይንን መጥኖ በጊዜው መጠጣት መልካም ነው።
28ወይን የልቡና ኀዘንን ያስረሳል፤
ለሚያለቅስና ለሚያዝን ሰውም ወይንን አጠጣው።
29ሰነፍ ሰው ወይን በጠጣ ጊዜ ክርክርን ያበዛል፥ ይስታል፥ ይበድላልም፤
የመጠጥ ብዛት ኀይልን አያስገኝም፤ ቍስልንም አያሳጣም።
30ወይን ጠጥቶ ሳለ ባልንጀራህን አትቈጣው፤
ልቡ ደስ ብሎት ሳለም አታሳዝነው፤
የምትነቅፈውንም አትንገረው፤
እርሱ ሰክሮ ሳለ ጉዳይህን አትለምነው፤ አትዘብዝበውም።