መጽሐፈ ሲራክ 32
32
1ሕጉን የሚጠብቅ ሰው መባ ያገባል።
2ትእዛዙን የሚሰማ ሰውም ለድኅነቱ መሥዋዕትን ይሠዋል።
3ስንዴ የሚያገባ ሰው ዋጋውን ይመልሳል።
4ምጽዋትን የሚመጸውት ሰውም የምስጋና መሥዋዕትን ሠዋ።
5የእግዚአብሔር ፈቃዱ ክፉ እንዳትሠራ ነው፤
ፈቃዱም ከበደል ትርቅ ዘንድ ነው።
6ወደ እግዚአብሔር ፊት ባዶህን አትግባ።
7ይህን ሁሉ ስለ ትእዛዙ አድርግ።
8የጻድቅ ሰው መሥዋዕት ምሠዊያውን ያለመልመዋል፤
መዓዛውም ወደ ልዑል ፊት ይደርሳል።
9የጻድቅ ሰው መሥዋዕት ቅዱስ ነው፤
ስም አጠራሩም ሁሉ አይዘነጋበትም።
10በደስታ ዐይን እግዚአብሔርን አመስግነው፤
ከመጀመሪያ አዝመራህም ዐሥራት ማግባትን አትተው።
11የሰጠህን ሁሉ ፊትህን ደስ እያለው ስጠው፤
ደስ እያለህም የአዝመራህን ዐሥራት አግባ።
12እንደ ክብሩ ብዛት መጠን ለእግዚአብሔር መባእህን አግባ፤
በእጅህ ከአገኘኸውም በመልካም ዐይን አግባለት።
13እግዚአብሔር ዋጋህን ይመልስልሃልና፤
ሰባት እጥፍ አድርጎም ይሰጥሃልና፤
14አይቀበልልህምና መማለጃን አታግባለት።
15እግዚአብሔር የእውነት ዳኛ ነውና፥
ፊትን አይቶም አያዳላምና የዐመፃ መሥዋዕትን የሚቀበል አይምሰልህ።
16ድሃውን ስለ ችግሩ አይለየውም፤
የተበደለ ሰውንም ጩኸት ይሰማል።
17የሙት ልጅ ልመናን ቸል አይልም፤
ባልቴት ሴትንም የሚያስለቅሳት ሰው ቢኖር፥
18እንባንም በፊትዋ ላይ ብታወርድ፥
19እንደዚሁ ባስለቀሳት ሰው ላይ እንባ ይወርዳል።
20በእውነት የሚያገለግለውን ሰው ይቀበለዋል፤
ጸሎቱም እስከ ደመና ትደርሳለች።
21የትሑት ጸሎት ከደመና ታልፋለች፥
ወደ እርሱ እስክትደርስ አትመለስም፥
እግዚአብሔርም እስከሚያያት ድረስ አትመለስም።
22ለጻድቃን ይፈርድላቸዋል፤ ይበቀልላቸዋልም፤
እግዚአብሔር ለእነርሱ አይዘገይም፤
ክፉዎችን ወገባቸውን እስኪቀጠቅጥ ድረስ ስለ እነርሱ ፈጽሞ አይታገሥም።
23አሕዛብን ይበቀላቸዋል፤ ዐመፀኞችንም ሁሉ ያጠፋቸዋል፤
የኀጢአተኞችንም በትር ይሰብራል።
24ለሰው ሁሉ እንደ ሥራው ይከፍለዋል።
25ስለ ሰዎችም ሁሉ እንደ ሥራቸውና
እንደ አካሄዳቸው ፍዳውን ይከፍላቸዋል።
የወገኖቹን በቀል ይመልሳልና፥ በቸርነቱም ደስ ያሰኛቸዋልና።
26በመከራ ጊዜ የሚገኝ ምሕረት
በቃጠሎ ጊዜ ዝናም እንደ ያዘ ደመና ነው።
Currently Selected:
መጽሐፈ ሲራክ 32: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
መጽሐፈ ሲራክ 32
32
1ሕጉን የሚጠብቅ ሰው መባ ያገባል።
2ትእዛዙን የሚሰማ ሰውም ለድኅነቱ መሥዋዕትን ይሠዋል።
3ስንዴ የሚያገባ ሰው ዋጋውን ይመልሳል።
4ምጽዋትን የሚመጸውት ሰውም የምስጋና መሥዋዕትን ሠዋ።
5የእግዚአብሔር ፈቃዱ ክፉ እንዳትሠራ ነው፤
ፈቃዱም ከበደል ትርቅ ዘንድ ነው።
6ወደ እግዚአብሔር ፊት ባዶህን አትግባ።
7ይህን ሁሉ ስለ ትእዛዙ አድርግ።
8የጻድቅ ሰው መሥዋዕት ምሠዊያውን ያለመልመዋል፤
መዓዛውም ወደ ልዑል ፊት ይደርሳል።
9የጻድቅ ሰው መሥዋዕት ቅዱስ ነው፤
ስም አጠራሩም ሁሉ አይዘነጋበትም።
10በደስታ ዐይን እግዚአብሔርን አመስግነው፤
ከመጀመሪያ አዝመራህም ዐሥራት ማግባትን አትተው።
11የሰጠህን ሁሉ ፊትህን ደስ እያለው ስጠው፤
ደስ እያለህም የአዝመራህን ዐሥራት አግባ።
12እንደ ክብሩ ብዛት መጠን ለእግዚአብሔር መባእህን አግባ፤
በእጅህ ከአገኘኸውም በመልካም ዐይን አግባለት።
13እግዚአብሔር ዋጋህን ይመልስልሃልና፤
ሰባት እጥፍ አድርጎም ይሰጥሃልና፤
14አይቀበልልህምና መማለጃን አታግባለት።
15እግዚአብሔር የእውነት ዳኛ ነውና፥
ፊትን አይቶም አያዳላምና የዐመፃ መሥዋዕትን የሚቀበል አይምሰልህ።
16ድሃውን ስለ ችግሩ አይለየውም፤
የተበደለ ሰውንም ጩኸት ይሰማል።
17የሙት ልጅ ልመናን ቸል አይልም፤
ባልቴት ሴትንም የሚያስለቅሳት ሰው ቢኖር፥
18እንባንም በፊትዋ ላይ ብታወርድ፥
19እንደዚሁ ባስለቀሳት ሰው ላይ እንባ ይወርዳል።
20በእውነት የሚያገለግለውን ሰው ይቀበለዋል፤
ጸሎቱም እስከ ደመና ትደርሳለች።
21የትሑት ጸሎት ከደመና ታልፋለች፥
ወደ እርሱ እስክትደርስ አትመለስም፥
እግዚአብሔርም እስከሚያያት ድረስ አትመለስም።
22ለጻድቃን ይፈርድላቸዋል፤ ይበቀልላቸዋልም፤
እግዚአብሔር ለእነርሱ አይዘገይም፤
ክፉዎችን ወገባቸውን እስኪቀጠቅጥ ድረስ ስለ እነርሱ ፈጽሞ አይታገሥም።
23አሕዛብን ይበቀላቸዋል፤ ዐመፀኞችንም ሁሉ ያጠፋቸዋል፤
የኀጢአተኞችንም በትር ይሰብራል።
24ለሰው ሁሉ እንደ ሥራው ይከፍለዋል።
25ስለ ሰዎችም ሁሉ እንደ ሥራቸውና
እንደ አካሄዳቸው ፍዳውን ይከፍላቸዋል።
የወገኖቹን በቀል ይመልሳልና፥ በቸርነቱም ደስ ያሰኛቸዋልና።
26በመከራ ጊዜ የሚገኝ ምሕረት
በቃጠሎ ጊዜ ዝናም እንደ ያዘ ደመና ነው።