መጽሐፈ ሲራክ 18
18
1ለዘለዓለም ሕያው የሆነ እርሱ ሁሉን በአንድነት ፈጠረ።
2እውነተኛ እግዚአብሔር ብቻ ነው።
3ሥራውን ያውቅ ዘንድ ማንንም አላሰናበተውም፤
የገናናነቱንስ ፍለጋ ማን መርምሮ ያውቃል?
4ከሀሊነቱንስ ማን መርምሮ ያውቃል?
ቸርነቱንስ ማን ጠንቅቆ ይናገራል?
5መጨመርም የለም፤ መቀነስም የለም፤
የእግዚአብሔርን የጌትነቱን ፍለጋ የሚያገኝ የለም።
6ሰውን በፈጠረው ጊዜ ያንጊዜ ያዝዘዋል፤
ዘመኑንም ባስጨረሰው ጊዜ ያንጊዜ ያሳርፈዋል።
7ሰው ምንድን ነው? ጥቅሙስ ምንድን ነው?
8በጎነቱ ምንድን ነው? ክፋቱስ ምንድን ነው?
የዘመኑም ቍጥር ቢበዛ መቶ ዓመት ነው፤
9በባሕር ውስጥ እንደ አንዲት የውኃ ጠብታ፥ ከአሸዋውም ሁሉ እንደ አንዲት የአሸዋ ቅንጣት፥
እንዲሁ በዘለዓለማዊነት ዓመታት ዘንድ የሰው ዘመኑ ጥቂት ነው።
10ስለዚህ ነገር እግዚአብሔር ይታገሣቸዋል።
ምሕረቱን አሳደረባቸው።
11ፍጻሜያቸው ክፉ እንደ ሆነ አይቶ ዐወቃቸው፤
ምሕረቱን እንዲሁ አብዝትዋልና።
12ሰው ባልንጀራውን ብቻ ይቅር ይላል፥
እግዚአብሔር ግን ፍጥረቱን ሁሉ ይቅር ይላል፤
13ይቈጣል፥ ይገርፋል፥ ይቅር ይላል፥
እረኛም መንጋውን እንዲመልስ ይመልሳል።
በተግሣጹ የሚታገሡትን፥ ሕጉንም የሚከተሉትን ሰዎች ይቅር ይላቸዋል።
የተወደደ ምጽዋት
14ልጄ ሆይ፥ በደስታህ መካከል ኀዘንን አታስገባ፤
በምትስጠውም ሁሉ ክፉ ነገርን አትናገር።
15ዝናም ዋዕይን የሚያቀዘቅዘው አይደለምን?
እንዲሁ በጎ ቃል ከመስጠት ይሻላል።
16እነሆ እንግዲህ ከመስጠት መልካም ቃል አይሻልምን?
ሁለቱም ሁሉ በጻድቅ ሰው ዘንድ ይገኛሉ።
17ንፉግ ልቡናውን ደስ ሳይለው ይሰጣል።
ሰነፍም ይላገዳል አያመሰግንምም።
18ሳትናገር ተረዳ፥ ሳትታመምም ዳን።
19ሳይፈረድብህ ራስህን መርምር፤
በመከራህም ጊዜ ይቅርታን ታገኛለህ።
20ሳትደክም ራስህን አዋርድ፥
በበደልህም ጊዜ ንስሓ ግባ።
21ስእለትህን ፈጥነህ ስጥ፤
ሳትሞትም ጽድቅን ሥራት።
22ሳትሳልም አስቀድመህ ስእለትህን አዘጋጅ፤
እግዚአብሔርን እንደሚፈታተነው ሰው አትሁን።
23በተቈጣህም ጊዜ የሞትን ቀን ዐስብ፤
የፍዳህንም ቀን ዐስብ፤ ንስሓም ግባ ጸልይም።#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ፊቱን በመመለስ በመጨረሻ ስለሚሆነው ቍጣና የበቀል ቀን ዐስብ” ይላል።
24በጥጋብህ ወራት የረኃብን ወራት ዐስብ።
በተድላህም ወራት የችግርን ወራት ዐስብ።
25ኑሮ ከጧት እስከ ማታ ድረስ ትለዋወጣለችና፥
ሁሉም በእግዚአብሔር ዘንድ አንድ ጊዜ ፈጥኖ ይደረጋልና።
26ብልህ ሰው ግን ፈርቶ በሁሉ ይጠበቃል፤
ኀጢአት በሚሠራበትም ጊዜ ንስሓ ይገባል።
27አስተዋይ ሰው ሁሉ ጥበብን ያገኛታል፤
ያገኛትንም ሰው ታስመሰግነዋለች፥ ታስከብረዋለችም፥
28ነገር ዐዋቂዎች ራሳቸው በልቡናቸው ይራቀቃሉ፤
የተረዳ ምሳሌንም ይናገራሉ።
29አትሂድ፥ የኀጢአትንም ፈቃድ አትከተል፤
ከክፉ ፍትወትም ራቅ።
30ለሰውነትህ የምትወድደውን ከሰጠኻት፥
ጠላትህን በአንተ የጨከነ ታደርገዋለች።
31በተድላ ብዛት ደስ አይበልህ፤
ከእርስዋም ጋር ደስ ይልህ ዘንድ አትለምን።
32እንዳትያዝ አንተ ድሃ ሳለህ፥ በከረጢትህም ምንም ሳይኖርህ አትበደር።
Currently Selected:
መጽሐፈ ሲራክ 18: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
መጽሐፈ ሲራክ 18
18
1ለዘለዓለም ሕያው የሆነ እርሱ ሁሉን በአንድነት ፈጠረ።
2እውነተኛ እግዚአብሔር ብቻ ነው።
3ሥራውን ያውቅ ዘንድ ማንንም አላሰናበተውም፤
የገናናነቱንስ ፍለጋ ማን መርምሮ ያውቃል?
4ከሀሊነቱንስ ማን መርምሮ ያውቃል?
ቸርነቱንስ ማን ጠንቅቆ ይናገራል?
5መጨመርም የለም፤ መቀነስም የለም፤
የእግዚአብሔርን የጌትነቱን ፍለጋ የሚያገኝ የለም።
6ሰውን በፈጠረው ጊዜ ያንጊዜ ያዝዘዋል፤
ዘመኑንም ባስጨረሰው ጊዜ ያንጊዜ ያሳርፈዋል።
7ሰው ምንድን ነው? ጥቅሙስ ምንድን ነው?
8በጎነቱ ምንድን ነው? ክፋቱስ ምንድን ነው?
የዘመኑም ቍጥር ቢበዛ መቶ ዓመት ነው፤
9በባሕር ውስጥ እንደ አንዲት የውኃ ጠብታ፥ ከአሸዋውም ሁሉ እንደ አንዲት የአሸዋ ቅንጣት፥
እንዲሁ በዘለዓለማዊነት ዓመታት ዘንድ የሰው ዘመኑ ጥቂት ነው።
10ስለዚህ ነገር እግዚአብሔር ይታገሣቸዋል።
ምሕረቱን አሳደረባቸው።
11ፍጻሜያቸው ክፉ እንደ ሆነ አይቶ ዐወቃቸው፤
ምሕረቱን እንዲሁ አብዝትዋልና።
12ሰው ባልንጀራውን ብቻ ይቅር ይላል፥
እግዚአብሔር ግን ፍጥረቱን ሁሉ ይቅር ይላል፤
13ይቈጣል፥ ይገርፋል፥ ይቅር ይላል፥
እረኛም መንጋውን እንዲመልስ ይመልሳል።
በተግሣጹ የሚታገሡትን፥ ሕጉንም የሚከተሉትን ሰዎች ይቅር ይላቸዋል።
የተወደደ ምጽዋት
14ልጄ ሆይ፥ በደስታህ መካከል ኀዘንን አታስገባ፤
በምትስጠውም ሁሉ ክፉ ነገርን አትናገር።
15ዝናም ዋዕይን የሚያቀዘቅዘው አይደለምን?
እንዲሁ በጎ ቃል ከመስጠት ይሻላል።
16እነሆ እንግዲህ ከመስጠት መልካም ቃል አይሻልምን?
ሁለቱም ሁሉ በጻድቅ ሰው ዘንድ ይገኛሉ።
17ንፉግ ልቡናውን ደስ ሳይለው ይሰጣል።
ሰነፍም ይላገዳል አያመሰግንምም።
18ሳትናገር ተረዳ፥ ሳትታመምም ዳን።
19ሳይፈረድብህ ራስህን መርምር፤
በመከራህም ጊዜ ይቅርታን ታገኛለህ።
20ሳትደክም ራስህን አዋርድ፥
በበደልህም ጊዜ ንስሓ ግባ።
21ስእለትህን ፈጥነህ ስጥ፤
ሳትሞትም ጽድቅን ሥራት።
22ሳትሳልም አስቀድመህ ስእለትህን አዘጋጅ፤
እግዚአብሔርን እንደሚፈታተነው ሰው አትሁን።
23በተቈጣህም ጊዜ የሞትን ቀን ዐስብ፤
የፍዳህንም ቀን ዐስብ፤ ንስሓም ግባ ጸልይም።#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ፊቱን በመመለስ በመጨረሻ ስለሚሆነው ቍጣና የበቀል ቀን ዐስብ” ይላል።
24በጥጋብህ ወራት የረኃብን ወራት ዐስብ።
በተድላህም ወራት የችግርን ወራት ዐስብ።
25ኑሮ ከጧት እስከ ማታ ድረስ ትለዋወጣለችና፥
ሁሉም በእግዚአብሔር ዘንድ አንድ ጊዜ ፈጥኖ ይደረጋልና።
26ብልህ ሰው ግን ፈርቶ በሁሉ ይጠበቃል፤
ኀጢአት በሚሠራበትም ጊዜ ንስሓ ይገባል።
27አስተዋይ ሰው ሁሉ ጥበብን ያገኛታል፤
ያገኛትንም ሰው ታስመሰግነዋለች፥ ታስከብረዋለችም፥
28ነገር ዐዋቂዎች ራሳቸው በልቡናቸው ይራቀቃሉ፤
የተረዳ ምሳሌንም ይናገራሉ።
29አትሂድ፥ የኀጢአትንም ፈቃድ አትከተል፤
ከክፉ ፍትወትም ራቅ።
30ለሰውነትህ የምትወድደውን ከሰጠኻት፥
ጠላትህን በአንተ የጨከነ ታደርገዋለች።
31በተድላ ብዛት ደስ አይበልህ፤
ከእርስዋም ጋር ደስ ይልህ ዘንድ አትለምን።
32እንዳትያዝ አንተ ድሃ ሳለህ፥ በከረጢትህም ምንም ሳይኖርህ አትበደር።