የሉቃስ ወንጌል 3:2-6
የሉቃስ ወንጌል 3:2-6 አማ2000
ሐናና ቀያፋም ሊቃነ ካህናት በነበሩበት ወራት የእግዚአብሔር ቃል በምድረ በዳ ወደ ዘካርያስ ልጅ ወደ ዮሐንስ መጣ። ስለ ኀጢአት ስርየት ለንስሓ የሚያበቃ ጥምቀትን እየሰበከ በዮርዳኖስ አውራጃ ዞረ። በምድረ በዳ የሚጮኽ የአዋጅ ነጋሪ ድምፅ በነቢዩ በኢሳይያስ መጽሐፍ ቃል እንደ ተጻፈ፥ እንዲህ ሲል፥ “የእግዚአብሔርን መንገድ ጥረጉ፤ ጥርጊያውንም አስተካክሉ። ጐድጓዳው ሁሉ ይምላ፤ ተራራውም፥ ኮረብታውም ሁሉ ዝቅ ይበል፤ ሰንከልካላውም የቀና ጥርጊያ ይሁን፤ ወጣ ገባው መንገድም ይስተካከል። ሰውም ሁሉ የእግዚአብሔርን ትድግና ይይ።”


