መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ 1:8-10
መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ 1:8-10 አማ2000
የዚህ ሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፤ ነገር ግን የተጻፈበትን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም አንብበው፤ የዚያን ጊዜም መንገድህ ይቀናልሃል፤ አስተዋይም ትሆናለህ። እነሆ አዝዝሃለሁ፤ በምትሄድበት ሁሉ አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነውና ጽና፥ በርታ፤ አትፍራ፥ አትደንግጥም።” ኢያሱም የሕዝቡን ጻፎች እንዲህ ብሎ አዘዛቸው፦