የዮ​ሐ​ንስ ወን​ጌል 14:1-12

የዮ​ሐ​ንስ ወን​ጌል 14:1-12 አማ2000

“ልባ​ችሁ አይ​ደ​ን​ግጥ፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እመኑ፤ በእ​ኔም እመኑ። በአ​ባቴ ቤት ብዙ ማደ​ሪ​ያና ማረ​ፊያ አለ፤ እን​ዲ​ህስ ባይ​ሆን ኖሮ ቦታ ላዘ​ጋ​ጅ​ላ​ችሁ እሄ​ዳ​ለሁ እላ​ችሁ ነበር። ከሄ​ድ​ሁና ቦታ ካዘ​ጋ​ጀ​ሁ​ላ​ች​ሁም ዳግ​መኛ እመ​ጣ​ለሁ፤ እና​ን​ተም እኔ በአ​ለ​ሁ​በት ትኖሩ ዘንድ ወደ እኔ እወ​ስ​ዳ​ች​ኋ​ለሁ። ወዴ​ትም እን​ደ​ም​ሄድ ራሳ​ችሁ ታው​ቃ​ላ​ችሁ፤ መን​ገ​ዱ​ንም ታው​ቃ​ላ​ችሁ።” ቶማ​ስም፥ “ጌታዬ ሆይ፥ የም​ት​ሄ​ድ​በ​ትን የማ​ና​ውቅ እን​ግ​ዲህ መን​ገ​ዱን እን​ዴት እና​ው​ቃ​ለን?” አለው። ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስም እን​ዲህ አለው፥ “የእ​ው​ነ​ትና የሕ​ይ​ወት መን​ገድ እኔ ነኝ፤ በእኔ በኩል ካል​ሆነ በቀር ወደ አብ የሚ​መጣ የለም። እኔ​ንስ ብታ​ው​ቁኝ አባ​ቴ​ንም ባወ​ቃ​ች​ሁት ነበር፤ ከእ​ን​ግ​ዲህ ወዲህ ግን አው​ቃ​ች​ሁ​ታል፤ አይ​ታ​ች​ሁ​ት​ማል።” ፊል​ጶ​ስም፥ “ጌታ ሆይ፥ አብን አሳ​የ​ንና ይበ​ቃ​ናል” አለው። ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስም እን​ዲህ አለው፥ “ፊል​ጶስ፥ ይህን ያህል ዘመን አብ​ሬ​አ​ችሁ ስኖር አታ​ወ​ቀ​ኝ​ምን? እኔን ያየ አብን አየ፤ እን​ግ​ዲህ እን​ዴት አብን አሳ​የን ትላ​ለህ? እኔ በአብ እን​ዳ​ለሁ አብም በእኔ እን​ዳለ አታ​ም​ን​ምን? እኔ የም​ነ​ግ​ራ​ችሁ ይህ ቃልም ከራሴ የተ​ና​ገ​ር​ሁት አይ​ደ​ለም፤ በእኔ ያለ አብ እርሱ ይህን ሥራ ይሠ​ራ​ዋል እንጂ። እኔ በአብ እን​ዳ​ለሁ፥ አብም በእኔ እን​ዳለ እመኑ፤ ያለ​ዚ​ያም ስለ ሥራዬ እመ​ኑኝ። “እው​ነት እው​ነት እላ​ች​ኋ​ለሁ፤ በእኔ የሚ​ያ​ምን እኔ የም​ሠ​ራ​ውን ሥራ እር​ሱም ይሠ​ራል፤ ከዚ​ያም የሚ​በ​ልጥ ይሠ​ራል፤ እኔ ወደ አብ እሄ​ዳ​ለ​ሁና።