ትንቢተ ኤርምያስ 48
48
ስለ ሞአብ መጥፋት የተነገረ ትንቢት
1ስለ ሞአብ፤ የእስራኤል አምላክ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ናባው ጠፍታለችና ወዮላት! ቂርያታይም አፍራለች፤ ተይዛማለች፤ መጠጊያዋም አፍራለች፤ ደንግጣማለች። 2ከእንግዲህ ወዲህ የሞአብ ፈውስ#ዕብ. “ትምክህት” ይላል። የለም፤ በሐሴቦን ላይ፥ “ኑ ሕዝብ እንዳትሆን እናጥፋት” ብለው ክፉ ነገርን አስበውባታል። ፈጽሞ ትተዋለች፤ ከኋላዋ ሰይፍ ይመጣልና።#ዕብ. “መድሜን ሆይ አንቺ ደግሞ ትጠፊያለሽ ፤ ሰይፍም ያሳድድሻል” ይላል። 3መፍረስና ታላቅ ጥፋት የሚል የጩኸት ቃል ከሖሮናይም#“ከሖሮናይም” የሚለው በግእዝ የለም። ተሰማ። 4ሞአብ ጠፍታለች፤ ይህንም በሴጎር ተናገሩ።#ዕብ. “ልጆችዋም ጩኸትን አሰምተዋል” ይላል። 5በሎዊት ዓቀበት ልቅሶ እያለቀሱ ይወጣሉና፥ በሖሮናይምም መንገድ የመባባትን ጩኸት ሰምተዋል።
6“ሸሽታችሁ ራሳችሁን አድኑ፤ እንደ ሜዳ አህያ በምድረ በዳ ተቀመጡ፤ 7በሥራሽና በመዝገብሽ ታምነሻልና አንቺ ደግሞ ትያዢያለሽ፤ ካሞሽም ከካህናቱና ከአለቆቹ ጋር በአንድነት ይማረካል። 8እግዚአብሔርም እንደ ተናገረ፥ ጥፋት ወደ ከተማ ሁሉ ይመጣል፤ አንዲትም ከተማ አትድንም፤ ሸለቆውም ይጠፋል፤ ሜዳውም ይበላሻል። 9በርራ እንድትወጣ ለሞአብ ክንፍ ስጡአት፤ ከተሞችዋም ባድማ ይሆናሉ፤ የሚኖርባቸውም የለም። 10የእግዚአብሔርን ሥራ በቸልታ የሚያደርግ ርጉም ይሁን፤ ሰይፉንም ከደም የሚከለክል ርጉም ይሁን።
11“ሞአብ ከልጅነቷ ጀምራ ዐረፈች፤ በክብርዋም ቅምጥል ነበረች፤ ወይንዋም ከዕቃ ወደ ዕቃ አልተገላበጠም፤ ወደ ምርኮም አልሄደችም፤ ስለዚህ ቃናው በእርስዋ ውስጥ ቀርቶአል፤ መዓዛዋም አልተለወጠም። 12ስለዚህ እነሆ ጠማሞችን የምልክበት ዘመን ይመጣል፥ ይላል እግዚአብሔር፤ እነርሱም ይጠሙበታል፤ ጋኖቹንም ይቀጠቅጣሉ፤ ፊቀኖቹንም ይሰብራሉ። 13የእስራኤልም ቤት ይታመንባት ከነበረው ከቤቴል እንዳፈረ፥ እንዲሁ ሞአብ ከካሞሽ ታፍራለች። 14እናንተ፦ እኛ ኀያላን በሰልፍም ጽኑዓን ነን እንዴት ትላላችሁ? 15ሞዓብ ፈርሳለች፤ ከተሞቹዋም ጠፍተዋል፤ የተመረጡትም ጐልማሶችዋ ወደ መታረድ ወርደዋል፥ ይላል ስሙ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። 16የሞአብ ጥፋት ሊመጣ ቀርቦአል፤ መከራውም እጅግ ይፈጥናል። 17በዙሪያው ያላችሁ ሁሉ ስሙንም የምታውቁ ሁሉ፦ ታላቁ በትር፥ ጠንካራውም ሽመል፥ እንዴት ተሰበረ! ብላችሁ አልቅሱለት። 18በዲቦን የምትኖሪ ሆይ! ሞአብን የሚያጠፋ ወጥቶብሻልና፥ አምባሽንም ሰብሮአልና ከክብርሽ ውረጂ፤ በጭቃም ላይ ተቀመጪ። 19በአሮዔር የምትኖሪ ሆይ! በመንገድ አጠገብ ቆመሽ ተመልከቺ፤ የሸሸውንና ያመለጠውን፦ ምን ሆኖአል? ብለሽ ጠይቂው።
20“ሞአብ ፈርሳለችና አፈረች፤ አልቅሱ፥ ጩኹም፤ ሞአብ እንደ ጠፋች በአርኖን አውሩ። 21ፍርድ ይመጣል፤ በሜሶር ምድር፥ በኬሎን፥ በያሳና፥ በሜፍዓት#ግእዝ “ራባስ” ይላል። ላይ፤ 22በዲቦን፥ በናባው፥ በቤትዲብላታይም ላይ፥ 23በቂርያታይም፥ በቤትጋሙል፥ በቤትምዖን ላይ፥ 24በቂርዮት፥ በቦሶራ፥ በሞአብም ምድር ከተሞች ሁሉ ቅርብና ሩቅ በሆኑ ላይ ፍርድ መጥቶአል። 25የሞአብ ቀንድ ተሰበረ፤ እጁም ተቀጠቀጠ ይላል እግዚአብሔር።
ሞአብ እንደ ተዋረደ
26“በእግዚአብሔር ላይ ኰርቶአልና፥ አስክሩት፤ ሞአብም በትፋቱ ላይ ይንከባለላል፤ በእጁም ያጨበጭባል፤ ደግሞ መሳቂያ ይሆናል። 27እስራኤል ለአንተ መሳቂያ አልሆነምን? ወይስ በሌቦች መካከል ተገኝቶአልን? ስለ እርሱ በተናገርህ ጊዜ ራስህን ትነቀንቃለህ። 28በሞአብ የሚኖሩ ከተሞችን ትተው በዓለት ውስጥ ተቀመጡ፤ በገደል አፋፍም ቤቷን እንደምትሠራ እንደ ርግብ ሆኑ። 29የሞአብን ስድብ፥ የተዋረደውንም ብዙ ውርደቱን፥ ልቡናውንም ያስታበየበትን ትዕቢቱን ሰምተናል። 30እኔ ሥራውን አውቃለሁ ይላል እግዚአብሔር፤ እንደ ኀይሉም መጠን እንዲሁ ያደረገ አይደለም። 31ሰለዚህ ለሞአብ አለቅሳለሁ፤ ለሞአብም ሁሉ እጮኻለሁ፤ ለቂርሔሬስ ሰዎች አለቅሳለሁ። 32አንቺ የሴባማ ወይን ሆይ! የኢያዜርን ልቅሶ ለአንቺ አለቅሳለሁ፤ ቅርንጫፎችሽ ባሕርን ተሻግረዋል፤ ወደ ኢያዜርም ባሕር#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ከተማ” ይላል። ደርሰዋል፤ ሳይበስል#“ሳይበስል” የሚለው በዕብ. እና በግሪክ ሰባ. ሊ. የለም። በሰብልሽና በወይንሽ ላይ ጥፋት መጥቶአል። 33ሐሤትና ደስታ ከፍሬያማው እርሻና ከሞአብ ምድር ጠፍተዋል፤ ወይን ከመጥመቂያው ጠፍቶአል፤ በነግህ የሚጠምቁት የለም፤ በሠርክም የሚያደርጉት የእልልታ ድምፅ የለም። 34ከሐሴቦን ጩኸት እስከ ኤሊያሊና እስከ ኢያሳ ድረስ ድምፃቸውን ሰጥተዋል፤ ከሴጎር እስከ ሖሮናይምና እስከ ዔግላት ሺሊሺያ ድረስ ይደርሳል፤#ግእዝና ግሪክ ሰባ. ሊ. “የሦስት ዓመት ጊደር” ይላሉ። የኔምሬም ውኃ ደርቋልና። 35ሞአብንና በኮረብታው መስገጃ ላይ የሚሠዋውን፥ ለአማልክቱም የሚያጥነውን አጠፋለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር።
36“ያተረፈው ትርፉ ጠፍቶበታልና#“ያተረፈው ትርፉ ጠፍቶበታልና” የሚለው በግእዝ የለም። ስለዚህ ልቤ ለሞአብ እንደ እንቢልታ ይጮኻል፤ ልቤም ለቂርሔሬስ ሰዎች እንደ እንቢልታ ይጮኻል፤ 37በሰው ሁሉ ራስ ላይ ቡሃነት አለ፤ ጽሕማቸውን ሁሉ ይላጫሉ፤ እጆች ሁሉ ይንቀጠቀጣሉ፤ ሁሉም በወገባቸው ማቅን ይታጠቃሉ። 38ሞአብንም ለምንም እንደማይጠቅም ዕቃ ሰብሬአለሁና በሞአብ ሰገነት ሁሉ ላይ፥ በአደባባዩም ላይ ልቅሶ አለ፥” ይላል እግዚአብሔር። 39እንዴት ተለወጠች! ከእፍረትም የተነሣ ሞአብ ጀርባዋን እንዴት መለሰች! ሞአብም በዙሪያዋ ላሉት ሁሉ መሳቂያና መሳለቂያ ትሆናለች።
40እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፥ “እነሆ እንደ ንስር ይበርራል፤ ክንፉንም በሞአብ ላይ ይዘረጋል።#“እንደ ንስር ይበርራል ፤ ክንፉንም በሞአብ ላይ ይዘረጋል” የሚለው በግሪክ ሰባ. ሊ. የለም። 41ሐቄርዮት ተያዘች፤ አንባዎችዋም ተወስደዋል፤ በዚያም ቀን የሞአብ ኀያላን ልብ ምጥ እንደ ያዛት ሴት ልብ ይሆናል። 42ሞአብም በእግዚአብሔር ላይ ኰርታለችና ሕዝብ ከመሆን ትጠፋለች። 43በሞአብ የምትኖር ሆይ! ፍርሀትና ጕድጓድ፥ ወጥመድም በአንተ ላይ አሉ፥ ይላል እግዚአብሔር፤ 44እርስዋን በምጐበኝበት ዓመት በሞአብ ላይ ይህን አመጣለሁ፤ በፍርሀት የሸሸ በጕድጓድ ውስጥ ይወድቃል፤ ከጕድጓድም የወጣ በወጥመድ ይያዛል፤ ይላል እግዚአብሔር። 45ከሰልፍ የሸሹ ከሐሴቦን ጥላ በታች ቆመዋል፤ እሳት ከሐሴቦን፥ ነበልባልም ከሴዎን ወጥቶአል፤ የሞአብንም ማዕዘን፥ የሚጮኹ ልጆችንም ራስ በልቶአል። 46ሞአብ ሆይ! ወዮልሽ! የካሞሸ ወገን ጠፍቶአል፤ ወንዶች ልጆችሽ ተማርከው ተወስደዋልና፥ ሴቶች ልጆችሽም ወደ ምርኮ ሄደዋልና። 47ነገር ግን በኋለኛው ዘመን የሞአብን ምርኮ እመልሳለሁ፥” ይላል እግዚአብሔር። የሞዓብ ፍርድ እስከዚህ ድረስ ነው።#ከምዕ. 48 ከቍ. 45 እስከ 47 ያለው በግሪክ ሰባ. ሊ. የለም።
Currently Selected:
ትንቢተ ኤርምያስ 48: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
ትንቢተ ኤርምያስ 48
48
ስለ ሞአብ መጥፋት የተነገረ ትንቢት
1ስለ ሞአብ፤ የእስራኤል አምላክ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ናባው ጠፍታለችና ወዮላት! ቂርያታይም አፍራለች፤ ተይዛማለች፤ መጠጊያዋም አፍራለች፤ ደንግጣማለች። 2ከእንግዲህ ወዲህ የሞአብ ፈውስ#ዕብ. “ትምክህት” ይላል። የለም፤ በሐሴቦን ላይ፥ “ኑ ሕዝብ እንዳትሆን እናጥፋት” ብለው ክፉ ነገርን አስበውባታል። ፈጽሞ ትተዋለች፤ ከኋላዋ ሰይፍ ይመጣልና።#ዕብ. “መድሜን ሆይ አንቺ ደግሞ ትጠፊያለሽ ፤ ሰይፍም ያሳድድሻል” ይላል። 3መፍረስና ታላቅ ጥፋት የሚል የጩኸት ቃል ከሖሮናይም#“ከሖሮናይም” የሚለው በግእዝ የለም። ተሰማ። 4ሞአብ ጠፍታለች፤ ይህንም በሴጎር ተናገሩ።#ዕብ. “ልጆችዋም ጩኸትን አሰምተዋል” ይላል። 5በሎዊት ዓቀበት ልቅሶ እያለቀሱ ይወጣሉና፥ በሖሮናይምም መንገድ የመባባትን ጩኸት ሰምተዋል።
6“ሸሽታችሁ ራሳችሁን አድኑ፤ እንደ ሜዳ አህያ በምድረ በዳ ተቀመጡ፤ 7በሥራሽና በመዝገብሽ ታምነሻልና አንቺ ደግሞ ትያዢያለሽ፤ ካሞሽም ከካህናቱና ከአለቆቹ ጋር በአንድነት ይማረካል። 8እግዚአብሔርም እንደ ተናገረ፥ ጥፋት ወደ ከተማ ሁሉ ይመጣል፤ አንዲትም ከተማ አትድንም፤ ሸለቆውም ይጠፋል፤ ሜዳውም ይበላሻል። 9በርራ እንድትወጣ ለሞአብ ክንፍ ስጡአት፤ ከተሞችዋም ባድማ ይሆናሉ፤ የሚኖርባቸውም የለም። 10የእግዚአብሔርን ሥራ በቸልታ የሚያደርግ ርጉም ይሁን፤ ሰይፉንም ከደም የሚከለክል ርጉም ይሁን።
11“ሞአብ ከልጅነቷ ጀምራ ዐረፈች፤ በክብርዋም ቅምጥል ነበረች፤ ወይንዋም ከዕቃ ወደ ዕቃ አልተገላበጠም፤ ወደ ምርኮም አልሄደችም፤ ስለዚህ ቃናው በእርስዋ ውስጥ ቀርቶአል፤ መዓዛዋም አልተለወጠም። 12ስለዚህ እነሆ ጠማሞችን የምልክበት ዘመን ይመጣል፥ ይላል እግዚአብሔር፤ እነርሱም ይጠሙበታል፤ ጋኖቹንም ይቀጠቅጣሉ፤ ፊቀኖቹንም ይሰብራሉ። 13የእስራኤልም ቤት ይታመንባት ከነበረው ከቤቴል እንዳፈረ፥ እንዲሁ ሞአብ ከካሞሽ ታፍራለች። 14እናንተ፦ እኛ ኀያላን በሰልፍም ጽኑዓን ነን እንዴት ትላላችሁ? 15ሞዓብ ፈርሳለች፤ ከተሞቹዋም ጠፍተዋል፤ የተመረጡትም ጐልማሶችዋ ወደ መታረድ ወርደዋል፥ ይላል ስሙ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። 16የሞአብ ጥፋት ሊመጣ ቀርቦአል፤ መከራውም እጅግ ይፈጥናል። 17በዙሪያው ያላችሁ ሁሉ ስሙንም የምታውቁ ሁሉ፦ ታላቁ በትር፥ ጠንካራውም ሽመል፥ እንዴት ተሰበረ! ብላችሁ አልቅሱለት። 18በዲቦን የምትኖሪ ሆይ! ሞአብን የሚያጠፋ ወጥቶብሻልና፥ አምባሽንም ሰብሮአልና ከክብርሽ ውረጂ፤ በጭቃም ላይ ተቀመጪ። 19በአሮዔር የምትኖሪ ሆይ! በመንገድ አጠገብ ቆመሽ ተመልከቺ፤ የሸሸውንና ያመለጠውን፦ ምን ሆኖአል? ብለሽ ጠይቂው።
20“ሞአብ ፈርሳለችና አፈረች፤ አልቅሱ፥ ጩኹም፤ ሞአብ እንደ ጠፋች በአርኖን አውሩ። 21ፍርድ ይመጣል፤ በሜሶር ምድር፥ በኬሎን፥ በያሳና፥ በሜፍዓት#ግእዝ “ራባስ” ይላል። ላይ፤ 22በዲቦን፥ በናባው፥ በቤትዲብላታይም ላይ፥ 23በቂርያታይም፥ በቤትጋሙል፥ በቤትምዖን ላይ፥ 24በቂርዮት፥ በቦሶራ፥ በሞአብም ምድር ከተሞች ሁሉ ቅርብና ሩቅ በሆኑ ላይ ፍርድ መጥቶአል። 25የሞአብ ቀንድ ተሰበረ፤ እጁም ተቀጠቀጠ ይላል እግዚአብሔር።
ሞአብ እንደ ተዋረደ
26“በእግዚአብሔር ላይ ኰርቶአልና፥ አስክሩት፤ ሞአብም በትፋቱ ላይ ይንከባለላል፤ በእጁም ያጨበጭባል፤ ደግሞ መሳቂያ ይሆናል። 27እስራኤል ለአንተ መሳቂያ አልሆነምን? ወይስ በሌቦች መካከል ተገኝቶአልን? ስለ እርሱ በተናገርህ ጊዜ ራስህን ትነቀንቃለህ። 28በሞአብ የሚኖሩ ከተሞችን ትተው በዓለት ውስጥ ተቀመጡ፤ በገደል አፋፍም ቤቷን እንደምትሠራ እንደ ርግብ ሆኑ። 29የሞአብን ስድብ፥ የተዋረደውንም ብዙ ውርደቱን፥ ልቡናውንም ያስታበየበትን ትዕቢቱን ሰምተናል። 30እኔ ሥራውን አውቃለሁ ይላል እግዚአብሔር፤ እንደ ኀይሉም መጠን እንዲሁ ያደረገ አይደለም። 31ሰለዚህ ለሞአብ አለቅሳለሁ፤ ለሞአብም ሁሉ እጮኻለሁ፤ ለቂርሔሬስ ሰዎች አለቅሳለሁ። 32አንቺ የሴባማ ወይን ሆይ! የኢያዜርን ልቅሶ ለአንቺ አለቅሳለሁ፤ ቅርንጫፎችሽ ባሕርን ተሻግረዋል፤ ወደ ኢያዜርም ባሕር#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ከተማ” ይላል። ደርሰዋል፤ ሳይበስል#“ሳይበስል” የሚለው በዕብ. እና በግሪክ ሰባ. ሊ. የለም። በሰብልሽና በወይንሽ ላይ ጥፋት መጥቶአል። 33ሐሤትና ደስታ ከፍሬያማው እርሻና ከሞአብ ምድር ጠፍተዋል፤ ወይን ከመጥመቂያው ጠፍቶአል፤ በነግህ የሚጠምቁት የለም፤ በሠርክም የሚያደርጉት የእልልታ ድምፅ የለም። 34ከሐሴቦን ጩኸት እስከ ኤሊያሊና እስከ ኢያሳ ድረስ ድምፃቸውን ሰጥተዋል፤ ከሴጎር እስከ ሖሮናይምና እስከ ዔግላት ሺሊሺያ ድረስ ይደርሳል፤#ግእዝና ግሪክ ሰባ. ሊ. “የሦስት ዓመት ጊደር” ይላሉ። የኔምሬም ውኃ ደርቋልና። 35ሞአብንና በኮረብታው መስገጃ ላይ የሚሠዋውን፥ ለአማልክቱም የሚያጥነውን አጠፋለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር።
36“ያተረፈው ትርፉ ጠፍቶበታልና#“ያተረፈው ትርፉ ጠፍቶበታልና” የሚለው በግእዝ የለም። ስለዚህ ልቤ ለሞአብ እንደ እንቢልታ ይጮኻል፤ ልቤም ለቂርሔሬስ ሰዎች እንደ እንቢልታ ይጮኻል፤ 37በሰው ሁሉ ራስ ላይ ቡሃነት አለ፤ ጽሕማቸውን ሁሉ ይላጫሉ፤ እጆች ሁሉ ይንቀጠቀጣሉ፤ ሁሉም በወገባቸው ማቅን ይታጠቃሉ። 38ሞአብንም ለምንም እንደማይጠቅም ዕቃ ሰብሬአለሁና በሞአብ ሰገነት ሁሉ ላይ፥ በአደባባዩም ላይ ልቅሶ አለ፥” ይላል እግዚአብሔር። 39እንዴት ተለወጠች! ከእፍረትም የተነሣ ሞአብ ጀርባዋን እንዴት መለሰች! ሞአብም በዙሪያዋ ላሉት ሁሉ መሳቂያና መሳለቂያ ትሆናለች።
40እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፥ “እነሆ እንደ ንስር ይበርራል፤ ክንፉንም በሞአብ ላይ ይዘረጋል።#“እንደ ንስር ይበርራል ፤ ክንፉንም በሞአብ ላይ ይዘረጋል” የሚለው በግሪክ ሰባ. ሊ. የለም። 41ሐቄርዮት ተያዘች፤ አንባዎችዋም ተወስደዋል፤ በዚያም ቀን የሞአብ ኀያላን ልብ ምጥ እንደ ያዛት ሴት ልብ ይሆናል። 42ሞአብም በእግዚአብሔር ላይ ኰርታለችና ሕዝብ ከመሆን ትጠፋለች። 43በሞአብ የምትኖር ሆይ! ፍርሀትና ጕድጓድ፥ ወጥመድም በአንተ ላይ አሉ፥ ይላል እግዚአብሔር፤ 44እርስዋን በምጐበኝበት ዓመት በሞአብ ላይ ይህን አመጣለሁ፤ በፍርሀት የሸሸ በጕድጓድ ውስጥ ይወድቃል፤ ከጕድጓድም የወጣ በወጥመድ ይያዛል፤ ይላል እግዚአብሔር። 45ከሰልፍ የሸሹ ከሐሴቦን ጥላ በታች ቆመዋል፤ እሳት ከሐሴቦን፥ ነበልባልም ከሴዎን ወጥቶአል፤ የሞአብንም ማዕዘን፥ የሚጮኹ ልጆችንም ራስ በልቶአል። 46ሞአብ ሆይ! ወዮልሽ! የካሞሸ ወገን ጠፍቶአል፤ ወንዶች ልጆችሽ ተማርከው ተወስደዋልና፥ ሴቶች ልጆችሽም ወደ ምርኮ ሄደዋልና። 47ነገር ግን በኋለኛው ዘመን የሞአብን ምርኮ እመልሳለሁ፥” ይላል እግዚአብሔር። የሞዓብ ፍርድ እስከዚህ ድረስ ነው።#ከምዕ. 48 ከቍ. 45 እስከ 47 ያለው በግሪክ ሰባ. ሊ. የለም።