የማቴዎስ ወንጌል 15:7-11

የማቴዎስ ወንጌል 15:7-11 መቅካእኤ

እናንተ ግብዞች፥ ኢሳይያስ ስለ እናንተ እንዲህ ብሎ ትንቢት በትክክል ተናገረ፥ “ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል፥ ልቡ ግን ከእኔ እጅግ የራቀ ነው፤ የሰው ሥርዓት የሆነ ትምህርት እያስተማሩ በከንቱ ያመልኩኛል።” ሕዝቡንም ጠርቶ እንዲህ አላቸው “ስሙ አስተውሉም፤ ወደ አፍ የሚገባው ሰውን አያረክሰውም፤ ከአፍ የሚወጣው ግን ሰውን የሚያረክሰው ይህ ነው።”

ተዛማጅ ቪዲዮዎች