መልካም፣ ደስ የሚያሰኝና ፍጹም የሆነውን የእግዚአብሔር ፈቃድ ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በአእምሯችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ። እግዚአብሔር ለእያንዳንዳችሁ በሰጣችሁ እምነት መጠን ራሳችሁን በአግባቡ መዝኑ እንጂ፣ ከሆናችሁት በላይ ራሳችሁን ከፍ አድርጋችሁ እንዳታስቡ በተሰጠኝ ጸጋ እያንዳንዳችሁን እመክራለሁ። እያንዳንዳችን በአንዱ አካላችን ብዙ ብልቶች እንዳሉን፣ እነዚህም ብልቶች አንድ ዐይነት ተግባር እንደሌላቸው ሁሉ፣ እንዲሁም እኛ ብዙዎች ስንሆን በክርስቶስ አንድ አካል ነን። እያንዳንዳችንም የሌላው ብልት ነን። እንደ ተሰጠን ጸጋ የተለያዩ ስጦታዎች አሉን፤ ለአንዱ የተሰጠው ስጦታ ትንቢት መናገር ከሆነ፣ እንደ እምነቱ መጠን ይናገር። ማገልገል ቢሆን ያገልግል፤ ማስተማርም ከሆነ ያስተምር፤ መምከር ከሆነ ይምከር፤ ለሌላቸው መለገስ ከሆነም አብዝቶ ይለግስ፤ ማስተዳደር ከሆነም በትጋት ያስተዳድር፤ ምሕረት ማድረግ ከሆነም በደስታ ይማር።
ሮሜ 12 ያንብቡ
ያዳምጡ ሮሜ 12
ያጋሩ
ሁሉንም ሥሪቶች ያነጻጽሩ: ሮሜ 12:2-8
4 ቀናት
የሌሎችን ውዴታ ከመፈለግ እግዚአብሄርን ወደ መከተል እንዴት ትኩረትዎን መቀየር እንደሚችሉ ይወቁ። የኦሎምፒክ ሜዳሊያ አሸናፊ ዳንኤል ሮበርትስ የግል ታሪኮችን፣ ተግባራዊ ግንዛቤዎችን እና ቅዱሳት መጻሕፍትን አካፍሏል። ነፃነት ታገኛላችሁ እና ለእግዚአብሔር ክብር መኖርን ይማራሉ, ለአለም ማረጋገጫ አይደለም. ይህ የ 4-ቀን እቅድ ሰላምን እና አላማን ያቀፈ "የአትሌቶች ውድድር" አካል ነው.
ጥቅሶችን ያስቀምጡ፣ ያለበይነመረብ ያንብቡ፣ አጫጭር የትምህርት ቪዲዮዎችን ይመልከቱ እና ሌሎችም!
ቤት
መጽሐፍ ቅዱስ
እቅዶች
ቪዲዮዎች