ኢየሱስም ከዚያ እንደ ሄደ ሁለት ዐይነ ስውሮች፣ “የዳዊት ልጅ፤ ማረን!” በማለት እየጮኹ ተከተሉት። ዐይነ ስውሮቹም ኢየሱስ ወደ ገባበት ቤት ተከትለው ገቡ፤ ኢየሱስም፣ “ዐይናችሁን ላበራላችሁ እንደምችል ታምናላችሁ?” ሲል ጠየቃቸው። እነርሱም፣ “አዎን፣ ጌታ ሆይ፤” ብለው መለሱለት። ከዚያም ኢየሱስ ዐይኖቻቸውን ዳስሶ፣ “እንደ እምነታችሁ ይሁንላችሁ” አላቸው። ዐይኖቻቸውም በሩ፤ ኢየሱስም፣ “ይህን ማንም እንዳያውቅ” ብሎ በጥብቅ አስጠነቀቃቸው።
ማቴዎስ 9 ያንብቡ
ያዳምጡ ማቴዎስ 9
ያጋሩ
ሁሉንም ሥሪቶች ያነጻጽሩ: ማቴዎስ 9:27-30
12 ቀናት
ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረበት ጊዜ ሰዎችን ሲፈውስ ኃይሉንና ርኅራኄውን ያሳየበትን መንገድ መርምር። አንድ አጭር ቪዲዮ ኢየሱስ በእያንዳንዱ ቀን የፈወሰውን ባለ 12 ክፍል እቅድ ጎላ አድርጎ ያሳያል።
ጥቅሶችን ያስቀምጡ፣ ያለበይነመረብ ያንብቡ፣ አጫጭር የትምህርት ቪዲዮዎችን ይመልከቱ እና ሌሎችም!
ቤት
መጽሐፍ ቅዱስ
እቅዶች
ቪዲዮዎች