ከእነርሱም አንዱ መፈወሱን ባየ ጊዜ በታላቅ ድምፅ እግዚአብሔርን እያከበረ ተመለሰ፤ በኢየሱስም እግር ላይ በፊቱ ተደፍቶ አመሰገነው፤ ይህም ሰው ሳምራዊ ነበረ። ኢየሱስም እንዲህ ሲል ጠየቀው፤ “የነጹት ዐሥር ሰዎች አልነበሩምን? ታዲያ፣ ዘጠኙ የት ደረሱ? ከዚህ ከባዕድ ሰው በቀር ተመልሰው እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑ የሉም ማለት ነውን?” ሰውየውንም፣ “ተነሥተህ ሂድ፤ እምነትህ አድኖሃል” አለው። ፈሪሳውያን የእግዚአብሔር መንግሥት መቼ እንደምትመጣ ኢየሱስን በጠየቁት ጊዜ እንዲህ ሲል መለሰላቸው፤ “የእግዚአብሔር መንግሥት በሚታዩ ምልክቶች አትመጣም፤
ሉቃስ 17 ያንብቡ
ያዳምጡ ሉቃስ 17
ያጋሩ
ሁሉንም ሥሪቶች ያነጻጽሩ: ሉቃስ 17:15-20
12 ቀናት
ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረበት ጊዜ ሰዎችን ሲፈውስ ኃይሉንና ርኅራኄውን ያሳየበትን መንገድ መርምር። አንድ አጭር ቪዲዮ ኢየሱስ በእያንዳንዱ ቀን የፈወሰውን ባለ 12 ክፍል እቅድ ጎላ አድርጎ ያሳያል።
ጥቅሶችን ያስቀምጡ፣ ያለበይነመረብ ያንብቡ፣ አጫጭር የትምህርት ቪዲዮዎችን ይመልከቱ እና ሌሎችም!
ቤት
መጽሐፍ ቅዱስ
እቅዶች
ቪዲዮዎች