ኢዮብ 25
25
በልዳዶስ
1ሹሐዊውም በልዳዶስ እንዲህ ሲል መለሰ፤
2“ገዥነትና ግርማ የእግዚአብሔር ናቸው፤
በሰማይም ከፍታ ሥርዐትን ያደርጋል።
3ሰራዊቱ ሊቈጠር ይችላልን?
ብርሃኑስ የማይወጣው በማን ላይ ነው?
4ሰው በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ ይሆን ዘንድ፣
ከሴትስ የተወለደ ንጹሕ ይሆን ዘንድ ይችላልን?
5በፊቱ ጨረቃ እንኳ ብሩህ ካልሆነች፣
ከዋክብትም ንጹሓን ካልሆኑ፣
6ይልቁን ከብል የሚቈጠር የሰው ልጅ፣
ትል የሆነውማ ሰው ምንኛ ያንስ!”
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.