1
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6:19-20
መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)
መቅካእኤ
ወይስ ሰውነታችሁ፥ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት፥ በውስጣችሁም የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ መሆኑን አታውቁም? እናንተም የራሳችሁ አይደላችሁም። በዋጋ ተገዝታችኋል፤ ስለዚህ በሰውነታችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።
Qhathanisa
Hlola 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6:19-20
2
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6:9-10
ወይስ ዐመፀኞች የእግዚአብሔርን መንግሥት እንደማይወርሱ አታውቁምን? አትሳሳቱ፤ ሴሰኞች ቢሆኑ ወይም ጣዖትን የሚያመልኩ ወይም አመንዝሮች ወይም ግብረ ሰዶም የሚፈጽሙ፥ ወይም ሌቦች ወይም ስግብግቦች ወይም ሰካራሞች ወይም ተሳዳቢዎች ወይም ነጣቂዎች የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም።
Hlola 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6:9-10
3
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6:18
ከዝሙት ሽሹ። ሰው የሚያደርገው ኃጢአት ሁሉ ከሰውነቱ ውጭ ነው፤ ዝሙትን የሚሠራ ግን በገዛ ሰውነቱ ላይ ኃጢአትን ይሠራል።
Hlola 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6:18
4
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6:12
“ሁሉ ተፈቅዶልኛል፤” ሁሉ ግን አይጠቅምም። ሁሉ ተፈቅዶልኛል፤ በእኔ ላይ ግን አንድ ነገር እንኳ አይሠለጥንብኝም።
Hlola 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6:12
5
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6:14
እግዚአብሔርም ጌታን ከሞት አስነሣ፥ እኛንም በኀይሉ ያስነሣናል።
Hlola 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6:14
Ikhaya
IBhayibheli
Amapulani
Amavidiyo