ትንቢተ ሚልክያስ መግቢያ
መግቢያ
ትንቢተ ሚልክያስ የተገኘው ከክርስቶስ ልደት በፊት በአምስተኛው ምእት ዓመት የኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ ዳግመኛ ከተሠራ በኋላ ነበር። ነቢዩ አጥብቆ የሚያሳስበው ካህናቱም ሆኑ ሕዝቡ ከእግዚአብሔር ጋር የገቡትን ቃል ኪዳን ማደስ እንዳለባቸው ነበር፤ የእግዚአብሔር ሕዝብ በአኗኗሩም ሆነ በአምልኮቱ መረን የተለቀቀና የተበላሸ እንደ ነበር ግልጥ ነው፤ ካህናቱና ሕዝቡ ተገቢውን መሥዋዕት ባለማቅረብና በሰጣቸውም መመሪያ ባለመኖር እግዚአብሔርን ለማታለል ይሞክሩ ነበር። ስለ ሆነም እግዚአብሔር መንገዱን ለማዘጋጀትና ቃል ኪዳኑን ለማወጅ መልእክተኛውን አስቀድሞ በመላክ በሕዝቡ ላይ ለመፍረድና ሕዝቡን ለማጥራት ይመጣል።
አጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት
1. ጌታ ለእስራኤል ሕዝብ ያለው ፍቅር (1፥1-5)
2. የእግዚአብሔር ፍርድ በካህናት ላይ (1፥6—2፥9)
2. የቃል ኪዳን መፍረስ (2፥10-17)
4. የጌታ መምጣት (3፥1-4)
5. እግዚአብሔርን ማታለል የማይገባ መሆኑ (3፥5-15)
6. የታማኞች መሸለምና የክፉዎች መቀጣት (3፥16—4፥6)
Actualmente seleccionado:
ትንቢተ ሚልክያስ መግቢያ: አማ05
Destacar
Compartir
Copiar
¿Quieres tener guardados todos tus destacados en todos tus dispositivos? Regístrate o inicia sesión
© The Bible Society of Ethiopia, 2005
© የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር፥ 1997
ትንቢተ ሚልክያስ መግቢያ
መግቢያ
ትንቢተ ሚልክያስ የተገኘው ከክርስቶስ ልደት በፊት በአምስተኛው ምእት ዓመት የኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ ዳግመኛ ከተሠራ በኋላ ነበር። ነቢዩ አጥብቆ የሚያሳስበው ካህናቱም ሆኑ ሕዝቡ ከእግዚአብሔር ጋር የገቡትን ቃል ኪዳን ማደስ እንዳለባቸው ነበር፤ የእግዚአብሔር ሕዝብ በአኗኗሩም ሆነ በአምልኮቱ መረን የተለቀቀና የተበላሸ እንደ ነበር ግልጥ ነው፤ ካህናቱና ሕዝቡ ተገቢውን መሥዋዕት ባለማቅረብና በሰጣቸውም መመሪያ ባለመኖር እግዚአብሔርን ለማታለል ይሞክሩ ነበር። ስለ ሆነም እግዚአብሔር መንገዱን ለማዘጋጀትና ቃል ኪዳኑን ለማወጅ መልእክተኛውን አስቀድሞ በመላክ በሕዝቡ ላይ ለመፍረድና ሕዝቡን ለማጥራት ይመጣል።
አጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት
1. ጌታ ለእስራኤል ሕዝብ ያለው ፍቅር (1፥1-5)
2. የእግዚአብሔር ፍርድ በካህናት ላይ (1፥6—2፥9)
2. የቃል ኪዳን መፍረስ (2፥10-17)
4. የጌታ መምጣት (3፥1-4)
5. እግዚአብሔርን ማታለል የማይገባ መሆኑ (3፥5-15)
6. የታማኞች መሸለምና የክፉዎች መቀጣት (3፥16—4፥6)
Actualmente seleccionado:
:
Destacar
Compartir
Copiar
¿Quieres tener guardados todos tus destacados en todos tus dispositivos? Regístrate o inicia sesión
© The Bible Society of Ethiopia, 2005
© የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር፥ 1997