2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች መግቢያ
መግቢያ
ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች የጻፈላቸው ሁለተኛው መልእክት የተጻፈው በቆሮንቶስ ከነበረችው ቤተ ክርስቲያን ጋር የነበረው ግንኙነት እጅግ አስቸጋሪ በሆነበት ጊዜ ነው። አንዳንድ የቤተ ክርስቲያን አባሎች ከበድ ያሉ ነቀፋዎችን የሰነዘሩበት ቢሆንም ጳውሎስ ዕርቅ ለመፍጠር ታላቅ ፍላጎት እንዳለው ያሳያል፤ ይህም በሚሆንበት ጊዜ ታላቅ ደስታ ሊሰማው እንደሚችል ይገልጣል።
በመልእክቱ መጀመሪያ ክፍል ላይ ጳውሎስ በቆሮንቶስ ከነበረችው ቤተ ክርስቲያን ጋር ስላለው ግንኙነት በመግለጥ በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ለተነሣው ነቀፋና ተቃውሞ ለምን ከረር ያለ መልስ እንደሰጣቸው ያስረዳል። ከዚህም ጋራ በማያያዝ ይህ የእርሱ ተግሣጽ ወደ ንስሓና ወደ ዕርቅ የመራቸው በመሆኑ የተሰማውን ደስታ ይገልጥላቸዋል። ቀጥሎም በይሁዳ ያሉትን ክርስቲያኖች ለመርዳት በለጋስነት እንዲሰጡ ያሳስባቸዋል። በመጨረሻዎቹ ምዕራፎች ጳውሎስ በሐዋርያነቱ ላይ ስለ ቀረበበት ክስ መከላከያ ይሰጣል። በቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን አንዳንድ ሰዎች ራሳቸውን እውነተኞች ሐዋርያት በማድረግ ጳውሎስ ሐሰተኛ ሐዋርያ ነው እያሉ ይከሱት ነበር።
አጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት
መቅድም (1፥1-11)
ጳውሎስና የቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን (1፥12—7፥16)
በይሁዳ ለሚገኙ ክርስቲያኖች ርዳታ (8፥1—9፥15)
ጳውሎስ ለሐዋርያዊ ሥልጣኑ ያቀረበው መከላከል (10፥1—13፥10)
ማጠቃለያ (13፥11-13)
ምዕራፍ
Zur Zeit ausgewählt:
2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች መግቢያ: መቅካእኤ
Markierung
Teilen
Kopieren
Möchtest du deine gespeicherten Markierungen auf allen deinen Geräten sehen? Erstelle ein kostenloses Konto oder melde dich an.
2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች መግቢያ
መግቢያ
ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች የጻፈላቸው ሁለተኛው መልእክት የተጻፈው በቆሮንቶስ ከነበረችው ቤተ ክርስቲያን ጋር የነበረው ግንኙነት እጅግ አስቸጋሪ በሆነበት ጊዜ ነው። አንዳንድ የቤተ ክርስቲያን አባሎች ከበድ ያሉ ነቀፋዎችን የሰነዘሩበት ቢሆንም ጳውሎስ ዕርቅ ለመፍጠር ታላቅ ፍላጎት እንዳለው ያሳያል፤ ይህም በሚሆንበት ጊዜ ታላቅ ደስታ ሊሰማው እንደሚችል ይገልጣል።
በመልእክቱ መጀመሪያ ክፍል ላይ ጳውሎስ በቆሮንቶስ ከነበረችው ቤተ ክርስቲያን ጋር ስላለው ግንኙነት በመግለጥ በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ለተነሣው ነቀፋና ተቃውሞ ለምን ከረር ያለ መልስ እንደሰጣቸው ያስረዳል። ከዚህም ጋራ በማያያዝ ይህ የእርሱ ተግሣጽ ወደ ንስሓና ወደ ዕርቅ የመራቸው በመሆኑ የተሰማውን ደስታ ይገልጥላቸዋል። ቀጥሎም በይሁዳ ያሉትን ክርስቲያኖች ለመርዳት በለጋስነት እንዲሰጡ ያሳስባቸዋል። በመጨረሻዎቹ ምዕራፎች ጳውሎስ በሐዋርያነቱ ላይ ስለ ቀረበበት ክስ መከላከያ ይሰጣል። በቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን አንዳንድ ሰዎች ራሳቸውን እውነተኞች ሐዋርያት በማድረግ ጳውሎስ ሐሰተኛ ሐዋርያ ነው እያሉ ይከሱት ነበር።
አጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት
መቅድም (1፥1-11)
ጳውሎስና የቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን (1፥12—7፥16)
በይሁዳ ለሚገኙ ክርስቲያኖች ርዳታ (8፥1—9፥15)
ጳውሎስ ለሐዋርያዊ ሥልጣኑ ያቀረበው መከላከል (10፥1—13፥10)
ማጠቃለያ (13፥11-13)
ምዕራፍ
Zur Zeit ausgewählt:
:
Markierung
Teilen
Kopieren
Möchtest du deine gespeicherten Markierungen auf allen deinen Geräten sehen? Erstelle ein kostenloses Konto oder melde dich an.