የYouVersion አርማ
መጽሐፍ ቅዱስእቅዶችቪዲዮዎች
መተግበሪያውን ያግኙ
የቋንቋ መምረጫ
የፍለጋ አዶ

Psalms 95:1-11

መዝሙር 95:1-11 - ኑ፤ ደስ እያለን ለእግዚአብሔር እንዘምር፤
በድነታችንም ዐለት እልል እንበል።
ምስጋና ይዘን ፊቱ እንቅረብ፤
በዝማሬም እናወድሰው።

እግዚአብሔር ታላቅ አምላክ ነውና፤
ከአማልክትም ሁሉ በላይ ታላቅ ንጉሥ ነው።
የምድር ጥልቆች በእጁ ናቸው፤
የተራራ ጫፎችም የርሱ ናቸው።
እርሱ ፈጥሯታልና ባሕር የርሱ ናት፤ እጁም የብስን አበጀ።

ኑ፤ እናምልከው፤ እንስገድለትም፤
በፈጣሪያችን በእግዚአብሔር ፊት እንንበርከክ፤
እርሱ አምላካችን ነውና፤
እኛም በእጁ ጥበቃ ሥር ያለን በጎቹ፣
የመሰማሪያውም ሕዝብ ነን።

ዛሬ ድምፁን ብትሰሙ፣
በምድረ በዳ በነበራችሁበት ቀን በማሳህ፣
በመሪባም እንዳደረጋችሁት፣ ልባችሁን አታደንድኑ።
ሥራዬን ቢያዩም፣
አባቶቻችሁ በዚያ ፈተኑኝ፤ ተፈታተኑኝም።
ያን ትውልድ አርባ ዓመት ሙሉ ተቈጣሁት፤
እኔም፣ “በልቡ የሳተ ሕዝብ ነው፤
መንገዴንም አላወቀም” አልሁ።
ስለዚህ እንዲህ ብዬ በቍጣዬ ማልሁ፣ “ፈጽሞ ወደ ዕረፍቴ አይገቡም።”

ኑ፤ ደስ እያለን ለእግዚአብሔር እንዘምር፤ በድነታችንም ዐለት እልል እንበል። ምስጋና ይዘን ፊቱ እንቅረብ፤ በዝማሬም እናወድሰው። እግዚአብሔር ታላቅ አምላክ ነውና፤ ከአማልክትም ሁሉ በላይ ታላቅ ንጉሥ ነው። የምድር ጥልቆች በእጁ ናቸው፤ የተራራ ጫፎችም የርሱ ናቸው። እርሱ ፈጥሯታልና ባሕር የርሱ ናት፤ እጁም የብስን አበጀ። ኑ፤ እናምልከው፤ እንስገድለትም፤ በፈጣሪያችን በእግዚአብሔር ፊት እንንበርከክ፤ እርሱ አምላካችን ነውና፤ እኛም በእጁ ጥበቃ ሥር ያለን በጎቹ፣ የመሰማሪያውም ሕዝብ ነን። ዛሬ ድምፁን ብትሰሙ፣ በምድረ በዳ በነበራችሁበት ቀን በማሳህ፣ በመሪባም እንዳደረጋችሁት፣ ልባችሁን አታደንድኑ። ሥራዬን ቢያዩም፣ አባቶቻችሁ በዚያ ፈተኑኝ፤ ተፈታተኑኝም። ያን ትውልድ አርባ ዓመት ሙሉ ተቈጣሁት፤ እኔም፣ “በልቡ የሳተ ሕዝብ ነው፤ መንገዴንም አላወቀም” አልሁ። ስለዚህ እንዲህ ብዬ በቍጣዬ ማልሁ፣ “ፈጽሞ ወደ ዕረፍቴ አይገቡም።”

መዝሙር 95:1-11

Psalms 95:1-11
YouVersion

በየቀኑ ከእግዚአብሔር ጋር የቅርብ ግንኙነት እንዲኖርዎ እንዲፈልጉ የሚያበረታታዎ እና የሚሞግትዎ።

አገልግሎት

ስለ

ሙያዎች

በጎ ፈቃደኛ

ብሎግ

ተጫን / ይንኩት

ጠቃሚ ማስፈንጠሪያዎች

እገዛ

ልገሳ

የመጽሐፍ ቅዱስ እትሞች

የድምጽ መጽሐፍ ቅዱስ

የመጽሐፍ ቅዱስ ቋንቋዎች

የዕለቱ ጥቅስ


የዲጂታል አገልግሎት

Life.Church
English (US)

©2025 Life.Church / YouVersion

የግለሰብነት መመሪያ / የግለሰብ አቋም መመሪያውሎች
የተጋላጭነት ገለጻ ፕሮግራም
ፌስቡክትዊተርኢንስታግራምዩትዩብፒንትረስት

ቤት

መጽሐፍ ቅዱስ

እቅዶች

ቪዲዮዎች