እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ቸርነትህ መጠን፣
ምሕረት አድርግልኝ፤
እንደ ርኅራኄህም ብዛት፣
መተላለፌን ደምስስ።
በደሌን ፈጽሞ ዕጠብልኝ፤
ከኀጢአቴም አንጻኝ።
እኔ መተላለፌን ዐውቃለሁና፤
ኀጢአቴም ዘወትር በፊቴ ነው።
በቃልህ ትጸድቅ፣
በፍርድህም ንጹሕ ትሆን ዘንድ፣
አንተን፣ በርግጥ አንተን ብቻ በደልሁ፤
በፊትህም ክፉ ነገር አደረግሁ።
ስወለድ ጀምሮ በደለኛ፣
ገና እናቴም ስትፀንሰኝ ኀጢአተኛ ነኝ።