Psalms 22:1-15

መዝሙር 22:1-15 - አምላኬ፣ አምላኬ ለምን ተውኸኝ?
እኔን ከማዳን፣
ከመቃተቴም ቃል ለምን ራቅህ?
አምላኬ ሆይ፤ በቀን ወደ አንተ እጮኻለሁ፤
አንተ ግን አልመለስህልኝም፤
በሌሊት እንኳ አላረፍሁም።

አንተ ግን ቅዱሱ ነጋሢ፤
የእስራኤልም ምስጋና ነህ።
አባቶቻችን በአንተ ታመኑ፤
ተማመኑብህ፤ አንተም ታደግሃቸው።
ወደ አንተ ጮኹ፤ ዳኑም፤
በአንተም ታመኑ፤ አላፈሩም።

እኔ ግን ትል እንጂ ሰው አይደለሁም፤
ሰው ያላገጠብኝ፣ ሕዝብም የናቀኝ ነኝ።
የሚያዩኝ ሁሉ ይሣለቁብኛል፤
ራሳቸውንም እየነቀነቁ እንዲህ እያሉ ይዘልፉኛል፤
“በእግዚአብሔር ተማምኗል፤
እንግዲህ እርሱ ያድነው፤
ደስ የተሠኘበትን፣
እስኪ ይታደገው።”

አንተ ግን ከማሕፀን አወጣኸኝ፤
በእናቴም ጡት ሳለሁ፣ መታመኛ ሆንኸኝ።
ከማሕፀን ስወጣም በአንተ ላይ ተጣልሁ፤
ከእናቴ ሆድ ጀምሮም አንተ አምላኬ ነህ።
መከራ እየተቃረበ ነውና፣
የሚረዳኝም የለምና፣
ከእኔ አትራቅ።

ብዙ ኰርማዎች ከበቡኝ፤
ኀይለኛ የባሳን በሬዎችም ዙሪያዬን ቆሙ።
እንደሚነጥቅና እንደሚያገሣ አንበሳ፣
አፋቸውን ከፈቱብኝ።
እንደ ውሃ ፈሰስሁ፤
ዐጥንቶቼም ሁሉ ከመጋጠሚያቸው ወለቁ፤
ልቤ እንደ ሰም ሆነ፤
በውስጤም ቀለጠ።
ጕልበቴ እንደ ገል ደረቀ፤
ምላሴ ከላንቃዬ ጋራ ተጣበቀ፤
ወደ ሞት ዐፈርም አወረድኸኝ።

አምላኬ፣ አምላኬ ለምን ተውኸኝ? እኔን ከማዳን፣ ከመቃተቴም ቃል ለምን ራቅህ? አምላኬ ሆይ፤ በቀን ወደ አንተ እጮኻለሁ፤ አንተ ግን አልመለስህልኝም፤ በሌሊት እንኳ አላረፍሁም። አንተ ግን ቅዱሱ ነጋሢ፤ የእስራኤልም ምስጋና ነህ። አባቶቻችን በአንተ ታመኑ፤ ተማመኑብህ፤ አንተም ታደግሃቸው። ወደ አንተ ጮኹ፤ ዳኑም፤ በአንተም ታመኑ፤ አላፈሩም። እኔ ግን ትል እንጂ ሰው አይደለሁም፤ ሰው ያላገጠብኝ፣ ሕዝብም የናቀኝ ነኝ። የሚያዩኝ ሁሉ ይሣለቁብኛል፤ ራሳቸውንም እየነቀነቁ እንዲህ እያሉ ይዘልፉኛል፤ “በእግዚአብሔር ተማምኗል፤ እንግዲህ እርሱ ያድነው፤ ደስ የተሠኘበትን፣ እስኪ ይታደገው።” አንተ ግን ከማሕፀን አወጣኸኝ፤ በእናቴም ጡት ሳለሁ፣ መታመኛ ሆንኸኝ። ከማሕፀን ስወጣም በአንተ ላይ ተጣልሁ፤ ከእናቴ ሆድ ጀምሮም አንተ አምላኬ ነህ። መከራ እየተቃረበ ነውና፣ የሚረዳኝም የለምና፣ ከእኔ አትራቅ። ብዙ ኰርማዎች ከበቡኝ፤ ኀይለኛ የባሳን በሬዎችም ዙሪያዬን ቆሙ። እንደሚነጥቅና እንደሚያገሣ አንበሳ፣ አፋቸውን ከፈቱብኝ። እንደ ውሃ ፈሰስሁ፤ ዐጥንቶቼም ሁሉ ከመጋጠሚያቸው ወለቁ፤ ልቤ እንደ ሰም ሆነ፤ በውስጤም ቀለጠ። ጕልበቴ እንደ ገል ደረቀ፤ ምላሴ ከላንቃዬ ጋራ ተጣበቀ፤ ወደ ሞት ዐፈርም አወረድኸኝ።

መዝሙር 22:1-15