የYouVersion አርማ
መጽሐፍ ቅዱስእቅዶችቪዲዮዎች
መተግበሪያውን ያግኙ
የቋንቋ መምረጫ
የፍለጋ አዶ

Isaiah 43:18-25

ኢሳይያስ 43:18-25 - “የቀደመውን ነገር አታስቡ፤
ያለፈውን እርሱ።
እነሆ፤ አዲስ ነገር አደርጋለሁ!
እርሱም አሁን ይበቅላል፤ አታስተውሉትምን?
በምድረ በዳም መንገድ አዘጋጃለሁ፤
በበረሓም ምንጭ አፈልቃለሁ፤
የምድረ በዳ አራዊት፣
ቀበሮና ጕጕት ያከብሩኛል፤
በምድረ በዳ ውሃ፣
በበረሓም ምንጭ እሰጣለሁና።
ለመረጥሁት ሕዝቤ ውሃ እሰጣለሁ፤
ለራሴ ያበጀሁት ሕዝብ
ምስጋናዬን ያውጅ ዘንድ ይህን አደርጋለሁ።

“ያዕቆብ ሆይ፤ አንተ ግን አልጠራኸኝም፤
እስራኤል ሆይ፤ የእኔ ነገር ታክቶሃል።
ለሚቃጠል መሥዋዕት በጎች አላመጣህልኝም፤
በመሥዋዕትህም አላከበርኸኝም።
በእህል ቍርባን እንድታገለግለኝ አላስቸገርሁህም፤
በዕጣን መሥዋዕትም አላሰለቸሁህም።
መልካም መዐዛ ያለው ከሙን አልገዛህልኝም፤
በመሥዋዕትህ ሥብ አላጠገብኸኝም፤
ነገር ግን በኀጢአትህ አስቸገርኸኝ፤
በበደልህም አደከምኸኝ።

“ስለ ራሴ ስል መተላለፍህን የምደመስስልህ፣
እኔ፣ እኔው ነኝ፤
ኀጢአትህን አላስባትም።

“የቀደመውን ነገር አታስቡ፤ ያለፈውን እርሱ። እነሆ፤ አዲስ ነገር አደርጋለሁ! እርሱም አሁን ይበቅላል፤ አታስተውሉትምን? በምድረ በዳም መንገድ አዘጋጃለሁ፤ በበረሓም ምንጭ አፈልቃለሁ፤ የምድረ በዳ አራዊት፣ ቀበሮና ጕጕት ያከብሩኛል፤ በምድረ በዳ ውሃ፣ በበረሓም ምንጭ እሰጣለሁና። ለመረጥሁት ሕዝቤ ውሃ እሰጣለሁ፤ ለራሴ ያበጀሁት ሕዝብ ምስጋናዬን ያውጅ ዘንድ ይህን አደርጋለሁ። “ያዕቆብ ሆይ፤ አንተ ግን አልጠራኸኝም፤ እስራኤል ሆይ፤ የእኔ ነገር ታክቶሃል። ለሚቃጠል መሥዋዕት በጎች አላመጣህልኝም፤ በመሥዋዕትህም አላከበርኸኝም። በእህል ቍርባን እንድታገለግለኝ አላስቸገርሁህም፤ በዕጣን መሥዋዕትም አላሰለቸሁህም። መልካም መዐዛ ያለው ከሙን አልገዛህልኝም፤ በመሥዋዕትህ ሥብ አላጠገብኸኝም፤ ነገር ግን በኀጢአትህ አስቸገርኸኝ፤ በበደልህም አደከምኸኝ። “ስለ ራሴ ስል መተላለፍህን የምደመስስልህ፣ እኔ፣ እኔው ነኝ፤ ኀጢአትህን አላስባትም።

ኢሳይያስ 43:18-25

Isaiah 43:18-25
YouVersion

በየቀኑ ከእግዚአብሔር ጋር የቅርብ ግንኙነት እንዲኖርዎ እንዲፈልጉ የሚያበረታታዎ እና የሚሞግትዎ።

አገልግሎት

ስለ

ሙያዎች

በጎ ፈቃደኛ

ብሎግ

ተጫን / ይንኩት

ጠቃሚ ማስፈንጠሪያዎች

እገዛ

ልገሳ

የመጽሐፍ ቅዱስ እትሞች

የድምጽ መጽሐፍ ቅዱስ

የመጽሐፍ ቅዱስ ቋንቋዎች

የዕለቱ ጥቅስ


የዲጂታል አገልግሎት

Life.Church
English (US)

©2025 Life.Church / YouVersion

የግለሰብነት መመሪያ / የግለሰብ አቋም መመሪያውሎች
የተጋላጭነት ገለጻ ፕሮግራም
ፌስቡክትዊተርኢንስታግራምዩትዩብፒንትረስት

ቤት

መጽሐፍ ቅዱስ

እቅዶች

ቪዲዮዎች