የፍለጋ ውጤቶች ለ፦ Luke 8:30

ዕዝራ 8:30 (NASV)

ከዚያም ካህናቱና ሌዋውያኑ ኢየሩሳሌም ወደሚገኘው ወደ አምላካችን ቤት እንዲሄድ የተመዘነውን ብር፣ ወርቅና ንዋያተ ቅድሳት ተረከቡ።

ምሳሌ 8:30 (NASV)

በዚያ ጊዜ ከጐኑ ዋና ባለሙያ ነበርሁ። ሁልጊዜ በፊቱ ሐሤት እያደረግሁ፣ ዕለት ተዕለት በደስታ እሞላ ነበር፤

ማቴዎስ 8:30 (NASV)

ከእነርሱ ትንሽ ራቅ ብሎ፣ የብዙ ዐሣማ መንጋ ተሰማርቶ ነበር።

ማርቆስ 8:30 (NASV)

ኢየሱስም ስለ እርሱ ለማንም እንዳይናገሩ አስጠነቀቃቸው።

ሉቃስ 8:30 (NASV)

ኢየሱስም፣ “ስምህ ማን ነው?” ብሎ ጠየቀው። እርሱም ብዙ አጋንንት ገብተውበት ስለ ነበር፣ “ሌጌዎን” አለው።

ዮሐንስ 8:30 (NASV)

ይህንም እንደ ተናገረ ብዙዎች በርሱ አመኑ።

ዘፀአት 8:30 (NASV)

ከዚያም ሙሴ ከፈርዖን ተለይቶ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ።

ዘሌዋውያን 8:30 (NASV)

ቀጥሎም ሙሴ በመቅቢያው ዘይትና በመሠዊያው ላይ ካለው ደም ጥቂት ወስዶ፣ በአሮንና በልብሱ እንዲሁም በአሮን ልጆችና በልብሳቸው ላይ ረጨ፤ በዚህም ሁኔታ አሮንንና ልብሱን፣ ልጆቹንና ልብሳቸውን ቀደሰ።

ኢያሱ 8:30 (NASV)

ከዚያም ኢያሱ በጌባል ተራራ ላይ ለእስራኤል አምላክ ለ እግዚአብሔር መሠዊያን ሠራ።

መሳፍንት 8:30 (NASV)

ጌዴዎን ብዙ ሚስቶች ስላገባ ሰባ ልጆች ነበሩት፤

ሮሜ 8:30 (NASV)

አስቀድሞ የወሰናቸውንም ጠራቸው፤ የጠራቸውንም አጸደቃቸው፤ ያጸደቃቸውንም አከበራቸው።

ሐዋርያት ሥራ 8:30 (NASV)

ፊልጶስም ፈጥኖ ወደ ሠረገላው ሄደ፤ ጃንደረባውም የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ሲያነብብ ሰምቶ፣ “ለመሆኑ፣ የምታነብበውን ታስተውለዋለህን?” አለው።

1 ነገሥት 8:30 (NASV)

ባሪያህና ሕዝብህ እስራኤል ወደዚህ ስፍራ ጸሎት በሚያቀርቡበት ጊዜ፣ ልመናቸውን ተቀበል፤ መኖሪያህ በሆነው በሰማይ ስማ፤ ሰምተህም ይቅር በል።

1 ዜና መዋዕል 8:30 (NASV)

የበኵር ልጁም አብዶን ይባል ነበር፤ የእርሱም ተከታዮች ጹር፣ ቂስ፣ ባኣል፣ ኔር፣ ናዳብ፣

ኢዮብ 30:8 (NASV)

ስማቸው የማይታወቅ ሞኞች ናቸው፤ ከምድሪቱም ተባርረዋል።

መዝሙር 30:8 (NASV)

እግዚአብሔር ሆይ፤ ወደ አንተ ተጣራሁ፤ ወደ ጌታም እንዲህ ብዬ ጮኽሁ፤

ምሳሌ 30:8 (NASV)

ሐሰትንና ሐሰት መናገርን ከእኔ አርቅልኝ፤ ድኽነትንም ሆነ ብልጽግናን አትስጠኝ፤ ብቻ የዕለት እንጀራዬን ስጠኝ።

ኢሳይያስ 30:8 (NASV)

አሁንም ሂድ፤ በሰሌዳ ላይ ጻፍላቸው፤ በጥቅልል መጽሐፍ ላይ ክተብላቸው፤ ለሚመጡትም ዘመናት፣ ለዘላለም ምስክር ይሆናል፤

ኤርምያስ 30:8 (NASV)

“ ‘በዚያ ቀን’ ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ፤ ‘በጫንቃቸው ላይ ያለውን ቀንበር እሰብራለሁ፤ እስራታቸውንም እበጥሳለሁ፤ ከእንግዲህ ባዕዳን አይገዟቸውም።

ሕዝቅኤል 30:8 (NASV)

በግብጽ ላይ እሳት ስጭር፣ ረዳቶቿ ሁሉ ሲደቅቁ፣ በዚያ ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ።

ዘፍጥረት 30:8 (NASV)

ራሔልም፣ “እኅቴን ብርቱ ትግል ገጥሜ አሸነፍሁ” አለች፤ ስሙንም ንፍታሌም ብላ አወጣችለት።

ዘፀአት 30:8 (NASV)

ምሽት ላይ መብራቶቹን በሚያበራበትም ጊዜ ዕጣኑን ማጠን አለበት፤ ይኸውም በሚመጡት ትውልዶች ሁሉ ዕጣኑ በ እግዚአብሔር ፊት ዘወትር እንዲጤስ ነው።

ዘኍልቍ 30:8 (NASV)

ሆኖም ባሏ ይህንኑ ሰምቶ ከከለከላት ግን ለመፈጸም የተሳለችውንም ሆነ አምልጧት ተናግራ ራሷን ግዴታ ውስጥ ያስገባችበትን ነገር ስለሚያስቀር እግዚአብሔር ከዚህ ነጻ ያደርጋታል።

ዘዳግም 30:8 (NASV)

አንተም ተመልሰህ ለ እግዚአብሔር ትታዘዛለህ፤ ዛሬ እኔ የማዝዝህን ትእዛዝ ሁሉ ትጠብቃለህ።

1 ሳሙኤል 30:8 (NASV)

ዳዊትም፣ “ይህን ወራሪ ሰራዊት ልከተለውን? እደርስባቸዋለሁን?” ሲል እግዚአብሔር ን ጠየቀ። እግዚአብሔር ም፣ “በርግጥ ትደርስባቸዋለህ፤ ምርኮውንም ትመልሳለህ፤ ተከተል” ሲል መለሰለት።