ማሕልየ መሓልይ 8:4 - Compare All Versions
ማሕልየ መሓልይ 8:4 አማ2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))
እናንተ የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት ሆይ፥ ወድዶ እስኪነሣ ድረስ ፍቅሬን እንዳትቀሰቅሱትና እንዳታስነሡት በምድረ በዳው ኀይልና ጽንዐት አምላችኋለሁ።
ማሕልየ መሓልይ 8:4 NASV (አዲሱ መደበኛ ትርጒም)
እናንተ የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት፤ ራሱ እስኪፈልግ ድረስ፣ ፍቅርን እንዳታስነሡት ወይም እንዳትቀሰቅሱት አማፅናችኋለሁ።
ማሕልየ መሓልይ 8:4 አማ54 (መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት))
እናንተ የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት ሆይ፥ እርሱ እስኪፈልግ ድረስ ፍቅርን እንዳታስነሡት እንዳታነሣሡትም አምላችኋለሁ።
ማሕልየ መሓልይ 8:4 አማ05 (አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም)
እናንተ የኢየሩሳሌም ቈነጃጅ ሆይ! ፍቅር ራሱ ወዶ እስኪነሣ ድረስ ቀስቅሳችሁ እንዳታስነሡት ዐደራ እላችኋለሁ።
ማሕልየ መሓልይ 8:4 መቅካእኤ (መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ))
እናንተ የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት ሆይ፥ እርሱ እስኪፈልግ ድረስ ፍቅርን እንዳታስነሡት እንዳታነሣሡትም አስምላችኋለሁ።