ኢሳይያስ 65:16 - Compare All Versions

ኢሳይያስ 65:16 አማ2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))

እን​ዲ​ሁም በም​ድር ላይ የተ​ባ​ረኩ ይሆ​ናሉ፤ እው​ነ​ተ​ኛ​ውን አም​ላክ ያመ​ሰ​ግ​ና​ሉና፥ በም​ድ​ርም ላይ በእ​ው​ነ​ተ​ኛው አም​ላክ ይም​ላ​ሉና፤ የቀ​ድ​ሞ​ው​ንም ጭን​ቀት ረስ​ተ​ዋ​ልና፤ በል​ቡ​ና​ቸ​ውም አያ​ስ​ቡ​ት​ምና።

ኢሳይያስ 65:16 NASV (አዲሱ መደበኛ ትርጒም)

ስለዚህ በምድሪቱ ላይ በረከትን የሚጠራ፣ በእውነት አምላክ ስም ይባረካል፤ በምድሪቱ መሐላን የሚምል፣ በእውነት አምላክ ስም ይምላል፤ ያለፉት ችግሮች ተረስተዋል፤ ከዐይኖቼም ተሰውረዋል።

ኢሳይያስ 65:16 አማ54 (መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት))

እንዲሁም በምድር ላይ የተባረከ በእውነት አምላክ ይባረካል፥ በምድርም ላይ የማለ በእውነት አምላክ ይምላል፥ የቀድሞው ጭንቀት ተረስቶአልና፥ ከዓይኔም ተሰውሮአልና።

ኢሳይያስ 65:16 አማ05 (አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም)

የቀድሞው ችግር ስለ ተረሳና ከዐይኔ ስለ ተሰወረ በሀገሪቱ በረከትን የሚለምን በእኔ በታማኙ እግዚአብሔር ስም ይለምናል፤ በሀገሪቱም የሚምሉ በእኔ በታማኙ እግዚአብሔር ስም ይምላሉ።”

ኢሳይያስ 65:16 መቅካእኤ (መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ))

እንዲሁም በምድር ላይ የተባረከ በእውነት አምላክ ይባረካል፥ በምድርም ላይ የማለ በእውነት አምላክ ይምላል፤ ምክንያቱም የቀድሞው ጭንቀት ተረስቶአል፥ ከዓይኔም ተሰውሮአል።