ዘፍጥረት 27:34 - Compare All Versions
ዘፍጥረት 27:34 አማ2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))
ዔሳውም የአባቱን ቃል በሰማ ጊዜ ታላቅ፥ እጅግም መራራ ጩኸት ጮኸ፤ አባቱንም፥ “አባቴ ሆይ፥ እኔንም ደግሞ ባርከኝ” አለው።
ዘፍጥረት 27:34 NASV (አዲሱ መደበኛ ትርጒም)
ዔሳው የአባቱን ቃል ሲሰማ፣ ድምፁን ከፍ በማድረግ ምርር ብሎ አለቀሰ፤ አባቱንም፣ “አባቴ ሆይ፤ እኔንም ደግሞ እባክህ መርቀኝ” አለው።
ዘፍጥረት 27:34 አማ54 (መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት))
ዔሳውም የአባቱን ቃል በሰማ ጊዜ ታላቅ እጅግም መራራ ጩኸት ጮኸ አባቱንም፦ አባቴ ሆይ እኔንም ደግሚ ባርከኝ አለው።
ዘፍጥረት 27:34 አማ05 (አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም)
ዔሳው ይህን በሰማ ጊዜ ድምፁን ከፍ በማድረግ ምርር ብሎ እያለቀሰ “አባቴ ሆይ! እኔንም መርቀኝ!” አለ።
ዘፍጥረት 27:34 መቅካእኤ (መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ))
ዔሳውም የአባቱን ቃል በሰማ ጊዜ ታላቅ እጅግም መራራ ጩኸት ጮኸ፥ አባቱንም፦ “አባቴ ሆይ፥ እኔንም ደግሞ ባርከኝ” አለው።