ዘፀአት 27:1-8

ዘፀአት 27:1-8 የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) (አማ2000)

“ርዝ​መቱ አም​ስት ክንድ፥ ወር​ዱም አም​ስት ክንድ መሠ​ዊ​ያን ከማ​ይ​ነ​ቅዝ ዕን​ጨት አድ​ርግ፤ አራት ማዕ​ዘ​ንም ይሁን፤ ከፍ​ታ​ውም ሦስት ክንድ ይሁን። በአ​ራ​ቱም ማዕ​ዘን ቀን​ዶ​ችን ታደ​ር​ጋ​ለህ፤ ቀን​ዶቹ ሥረ-ወጥ ይሁኑ፤ በና​ስም ለብ​ጣ​ቸው። ለመ​ሠ​ዊ​ያው ክዳን ሥራ​ለት፤ መሸ​ፈ​ኛ​ውን፥ ጽዋ​ዎ​ቹን፥ የሥጋ ሜን​ጦ​ዎ​ቹን፥ የእ​ሳት መጫ​ሪ​ያ​ዎ​ቹ​ንም አድ​ርግ። ዕቃ​ው​ንም ሁሉ ከናስ አድ​ርግ። ለመ​ሠ​ዊ​ያ​ውም እንደ መረብ ሆኖ የተ​ሠራ የናስ መከታ አድ​ር​ግ​ለት፤ ለመ​ከ​ታ​ውም አራት የናስ ቀለ​በት በአ​ራት ማዕ​ዘኑ አድ​ር​ግ​ለት። መከ​ታ​ውም እስከ መሠ​ዊ​ያው እኩ​ሌታ ይደ​ርስ ዘንድ ከመ​ሠ​ዊ​ያው እር​ከን በታች አኑ​ረው። ለመ​ሠ​ዊ​ያ​ውም ከማ​ይ​ነ​ቅዝ ዕን​ጨት መሎ​ጊ​ያ​ዎ​ችን ሠር​ተህ በናስ ለብ​ጣ​ቸው፤ መሎ​ጊ​ያ​ዎ​ቹም በቀ​ለ​በ​ቶች ውስጥ ይግቡ፤ መሠ​ዊ​ያ​ው​ንም ስት​ሸ​ከሙ መሎ​ጊ​ያ​ዎቹ በመ​ሠ​ዊ​ያው በሁ​ለት ወገን ይሁኑ። ሰሌ​ዳ​ውም ፍል​ፍል ይሁን፤ በተ​ራ​ራው እን​ዳ​ሳ​የ​ሁህ ምሳሌ እን​ዲሁ አድ​ርግ።

ዘፀአት 27:1-8 አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም (አማ05)

“ከግራር እንጨት መሠዊያ ሥራ፤ ርዝመቱ ሁለት ሜትር ከኻያ ሳንቲ ሜትር የጐኑ ስፋት ሁለት ሜትር ከኻያ ሳንቲ ሜትር ቁመቱም አንድ ሜትር ከሠላሳ ሳንቲ ሜትር ይሁን። በአራቱም ማእዘን ጫፍ ላይ ጠርበህ ቀንድ መሳይ ጒጦች አውጣ፤ ይህም ከመሠዊያው ጋር አብሮ የተሠራ ይሁን፤ እርሱም በነሐስ የተለበጠ ይሁን። ዐመድ የሚጠራቀምባቸውን ድስቶችን፥ የእሳት መጫሪያዎችን፥ ጐድጓዳ ሳሕኖችን፥ ሜንጦዎችንና ማንደጃዎችን አዘጋጅ፤ ሁሉም ከነሐስ የተሠሩ ይሁኑ። እንደ መረብ ሆኖ የተሠራ የነሐስ መከላከያ አብጅለት፤ ለመከላከያውም አራት የነሐስ ቀለበቶች በአራቱም ማእዘን አድርግለት። መከላከያም እስከ መሠዊያው እኩሌታ እንዲደርስ ከመሠዊያው ክፈፍ በታች አድርገው፤ ለመሠዊያው መሸከሚያ የሚሆኑ መሎጊያዎችንም ከግራር እንጨት ሠርተህ በነሐስ ለብጣቸው። መሠዊያውን መሸከም በሚያስፈልግበትም ጊዜ መሎጊያዎቹን ከመሠዊያው በእያንዳንዱ ጐን ባሉት ቀለበቶች ውስጥ አግባ። በተራራው ላይ ባሳየሁህ ዕቅድ መሠረት መሠዊያውን ከሳንቃዎች ሥራ፤ ውስጡም ባዶ ይሁን።