1 ዜና መዋዕል 4:9 - Compare All Versions
1 ዜና መዋዕል 4:9 አማ2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))
ያግቤጽም ከወንድሞቹ ይልቅ የተከበረ ነበረ፤ እናቱም፦ በጣር ወልጄዋለሁና ብላ ስሙን፦ ያግቤጽ ብላ ጠራችው።
1 ዜና መዋዕል 4:9 NASV (አዲሱ መደበኛ ትርጒም)
ያቤጽ ከወንድሞቹ ይልቅ የተከበረ ሰው ነበረ፤ እናቱም “በጣር የወለድሁት” ስትል ስሙን ያቤጽ አለችው።
1 ዜና መዋዕል 4:9 አማ54 (መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት))
ያቤጽም ከወንድሞቹ ይልቅ የተከበረ ነበረ፤ እናቱም “በጣር ወልጄዋለሁና” ብላ ስሙን “ያቤጽ” ብላ ጠራችው።
1 ዜና መዋዕል 4:9 አማ05 (አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም)
ከቤተሰቡ መካከል እጅግ የተከበረ ያዕቤጽ ተብሎ የሚጠራ አንድ ሰው ነበር፤ እናቱ እርሱን በወለደች ጊዜ ከባድ የምጥ ጣር ደርሶባት ስለ ነበር “ያዕቤጽ” የሚል ስም አወጣችለት፤
1 ዜና መዋዕል 4:9 መቅካእኤ (መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ))
ያቤጽም ከወንድሞቹ ይልቅ የተከበረ ነበረ፤ እናቱም፦ “በጣር ወልጄዋለሁና” ብላ ስሙን፦ ያቤጽ ብላ ጠራችው።