መጽ​ሐፈ ጥበብ 9

9
ሰሎ​ሞን ጥበ​ብን ለማ​ግ​ኘት የጸ​ለ​የው ጸሎት
1በፍ​ጹም ልቤም እን​ዲህ አልሁ፥ “የአ​ባ​ቶች አም​ላክ፥ የም​ሕ​ረት ጌታ፥ በቃ​ልህ ዓለ​ሙን ሁሉ የፈ​ጠ​ርኽ፤ 2በጥ​በ​ብ​ህም ሰውን በአ​ንተ የተ​ፈ​ጠ​ረ​ውን ፍጥ​ረት እን​ዲ​ገዛ፥ 3ዓለ​ሙ​ንም በቸ​ር​ነ​ትና በጽ​ድቅ እን​ዲ​ሠ​ራራ፥ በቅን ልቡ​ናም እን​ዲ​ፈ​ርድ ያደ​ረ​ግ​ኸው፥ 4በዙ​ፋ​ንህ የም​ት​ቀ​መጥ ጥበ​ብን ስጠኝ፥ ከባ​ሮ​ች​ህም ለይ​ተህ አት​ና​ቀኝ። 5እኔ ባሪ​ያ​ህና የሴት ባሪ​ያህ ልጅ፥ ኀይሌ የደ​ከመ ሰው፥ ዘመ​ኔም ያነሰ፥ ሕግ​ንና ፍር​ድ​ንም ለማ​ወቅ አነ​ስ​ተኛ ነኝና።
6“ከሰው ልጆ​ችም ፍጹም የሆነ ሰው ቢኖር፥ በአ​ንተ ዘን​ድም የም​ት​ገኝ ጥበብ ከእ​ርሱ ብት​ርቅ እርሱ እንደ ኢም​ንት በሆነ ነበር። 7አንተ ለሕ​ዝ​ብህ ንጉሥ፥ ለወ​ን​ዶች ልጆ​ች​ህና ለሴ​ቶች ልጆ​ች​ህም ገዢ አድ​ር​ገህ መረ​ጥ​ኸኝ። 8በቅ​ዱስ ተራ​ራህ ላይ ቤተ መቅ​ደስ፥ በማ​ረ​ፊ​ያ​ህም ሀገር ከጥ​ንት ጀምሮ ባዘ​ጋ​ጀ​ኸው በቅ​ድ​ስ​ናህ ማደ​ሪያ አም​ሳል መሠ​ዊያ እን​ዲ​ሠራ አዘ​ዝኽ። 9ሥራ​ህ​ንም የም​ታ​ውቅ ጥበብ ከአ​ንተ ጋር ነበ​ረች፤ ዓለ​ም​ንም በፈ​ጠ​ርኽ ጊዜ ነበ​ረች፤ በፊ​ትህ ደስ የሚ​ያ​ሰ​ኝ​ህም ምን እንደ ሆነ፥ ለት​እ​ዛ​ዝ​ህም የቀ​ናው ምን እንደ ሆነ ትረዳ ነበር። 10ተነ​ሥታ ትመጣ ዘንድ ከከ​በሩ ሰማ​ዮች ከጌ​ት​ነ​ትህ ዙፋን ወደኔ ላካት፤ ከእ​ኔም ጋራ ትኖ​ርና ትደ​ክም ዘንድ ደስ የሚ​ያ​ሰ​ኝ​ህም ምን እንደ ሆነ ዐውቅ ዘንድ ላካት። 11አንተ የም​ታ​ው​ቀ​ውን ሥራ ሁሉ ታው​ቃ​ለ​ችና ንጹሕ አድ​ርጋ ወደ ሥራ​ዎች ሁሉ ትም​ራኝ፤ በኀ​ይ​ሏም ትጠ​ብ​ቀኝ። 12ሥራዬ ሁሉ የተ​ወ​ደደ ይሁን፤ ወገ​ኖ​ች​ህ​ንም በእ​ው​ነት ልግዛ፤ ለአ​ባ​ቶች ዙፋ​ኖ​ችም የተ​ዘ​ጋ​ጀሁ ልሁን።
13“የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ምክር የሚ​ያ​ውቅ ሰው ማን ነው? እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሚ​ወ​ድ​ደ​ው​ንስ ዐስቦ የሚ​ያ​ውቅ ማን ነው? 14የሟ​ቾች ዐሳ​ባ​ቸው ፈራሽ ነውና፥ የእ​ኛም ዐሳብ ጐፃ​ጕፅ ነውና። 15የሚ​ፈ​ርስ ሥጋ ነፍ​ስን ያሸ​ን​ፋ​ታ​ልና፥ ይከ​ብ​ዳ​ታ​ል​ምና፥ ምድ​ራዊ ማደ​ሪ​ያም ልብን ይሸ​ፍ​ና​ልና። 16በብዙ ትጋ​ትና ግዳጅ፥ በጭ​ን​ቅም ብን​መ​ረ​ምር በም​ድር የሚ​ሠ​ራ​ውን ሥራ እና​ገ​ኛ​ለን፤ በእ​ጃ​ችን የም​ን​ዳ​ስ​ሰ​ው​ንም ሥራ በድ​ካም እና​ገ​ኛ​ለን። በሰ​ማይ ያለ​ውን ግን ማን መረ​መ​ረው? 17አንተ ጥበ​ብን የሰ​ጠ​ኸው፥ ቅዱስ መን​ፈ​ስ​ህ​ንም ወደ እርሱ ከላይ የላ​ክ​ህ​ለት ሰው ካል​ሆነ በቀር ምክ​ር​ህን ማን ዐወቀ? 18ስለ​ዚህ በዚህ ዓለም ያሉ ሰዎች መን​ገ​ዳ​ቸው ቀና​ላ​ቸው፥ ደስ የሚ​ያ​ሰ​ኝ​ህ​ንም ነገር ሰዎች ዐወቁ፥ በጥ​በ​ብም ዳኑ።”

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ