መጽ​ሐፈ ሲራክ 33

33
ስለ እስ​ራ​ኤል ድኅ​ነት የቀ​ረበ ጸሎት
1የኀ​ይል ሁሉ ፈጣሪ አቤቱ፥ ይቅር በለን፤ ተመ​ለ​ስ​ል​ንም።
2በአ​ሕ​ዛብ ሁሉ ላይ አን​ተን መፍ​ራ​ትን አሳ​ድር።
3ልዩ በሆኑ ወገ​ኖ​ችም ላይ እጅ​ህን አንሣ፤
ኀይ​ል​ህ​ንም ይዩ።
4እነ​ርሱ እያዩ በእኛ ዘንድ እንደ ተመ​ሰ​ገ​ንህ፥
እን​ደ​ዚሁ እኛ እያ​የን በእ​ነ​ርሱ ዘንድ ተመ​ስ​ገን።
5አቤቱ ያለ​አ​ንተ ሌላ ፈጣሪ የለ​ምና፥
እኛ እን​ዳ​ወ​ቅ​ንህ እነ​ር​ሱም ይወ​ቁህ።
6ተአ​ም​ራ​ት​ህን አሳይ፤
ጌት​ነ​ት​ህ​ንም ግለጥ።
7በእ​ጅህ ኀይል በቀ​ኝ​ህም ክብር፥
8ጥፋ​ትን አም​ጣ​ባ​ቸው፤
መቅ​ሠ​ፍ​ት​ንም ላክ​ባ​ቸው።
9ዐመ​ፀ​ኛ​ው​ንም አጥ​ፋው፤
ጠላ​ት​ንም ቀጥ​ቅ​ጠው።
10ድንቅ ሥራ​ህን ይነ​ግሩ ዘንድ የባ​ሮ​ች​ህን መሐላ አስብ፤
የሚ​ጠ​ፉ​ባ​ት​ንም ቀን ፈጥ​ነህ አድ​ር​ጋት።
11በቍ​ጣና በእ​ሳት ቅሠ​ፋ​ቸው፤
ከእ​ነ​ር​ሱም ያመ​ለ​ጡ​ትን አጥ​ፋ​ቸው፤
በወ​ገ​ኖ​ች​ህም ላይ ክፉ ያደ​ረጉ ሰዎ​ችን ሞት ያግ​ኛ​ቸው።
12ያለ እኛ ሌላ ሰው የለም የሚሉ የጠ​ላ​ቶ​ችን አለ​ቆች ራስ ስበር።
13የያ​ዕ​ቆ​ብን ልጆች ሁሉ ሰብ​ስ​ባ​ቸው።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ