መጽ​ሐፈ ሲራክ 26

26
የደግ ሴት ተግ​ባር
1ደግ ሴትን ባሏ ያመ​ሰ​ግ​ና​ታል፤#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ደግ ሚስት ያለ​ችው ብፁዕ ነው” ይላል።
የሕ​ይ​ወት ዘመ​ኑም እጥፍ ይሆ​ናል።
2ቅን ሴት ባሏን ደስ ታሰ​ኘ​ዋ​ለች፤
ዘመ​ኑ​ንም በሰ​ላም ይጨ​ር​ሳል።
3የደግ ሴት ዕድሏ ያማረ ነው፤
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ፈራ ሰው​ንም ወደ ዕድሉ ታደ​ር​ሰ​ዋ​ለች።
4የባ​ለ​ጸ​ጋ​ውም የድ​ሃ​ውም ልቡ የቀና ይሁን፤
ሁል​ጊ​ዜም ፊቱ የበራ ይሁን።
ስለ ክፉ ሴት
5በእ​ነ​ዚህ በሦ​ስቱ ነገ​ሮች ልቡ​ናዬ ደነ​ገ​ጠ​ብኝ፤
አራ​ተ​ኛ​ውም ፊቴን አስ​ፈ​ራኝ፤
ይኸ​ውም የከ​ተማ ሁከት፥ የአ​ሕ​ዛብ መዶ​ለት፥
የሐ​ሰት ምስ​ክር፤ እነ​ዚህ ሁሉ ሰውን ለሞት ያደ​ር​ሳሉ።
6ባሏን የም​ታ​ስ​ቀና ሴት የልብ ቍስል ናት፤ የሰ​ው​ነ​ትም ኀዘን ናት፤
በክፉ ሁሉ የም​ት​ስ​ተ​ካ​ከል የም​ላስ ጅራፍ ናት።
7ክፉ ሴት ውልቅ ውልቅ እን​ደ​ሚል፥ እንደ በሬ ቀን​በር ናት፤
እር​ስ​ዋ​ንም የሚ​ይዝ ሰው ጊንጥ እን​ደ​ሚ​ጨ​ብጥ ሰው ነው።
8ሰካ​ራም ሴት ታላቅ ጥፋት ናት።
ኀፍ​ረ​ት​ዋ​ንም አት​ሸ​ፍ​ንም፤
9የሴት ዝሙ​ትዋ በዐ​ይኗ ይታ​ወ​ቃል፤
በቅ​ን​ድ​ቧም ይታ​ወ​ቃል።
10ስታ ራሷን እን​ዳ​ታ​ጠፋ፥
ልጅ​ህን አጽ​ን​ተህ ጠብ​ቃት።
11ከአ​መ​ን​ዝራ ዐይን ጠብ​ቃት፤
ብት​በ​ድ​ል​ህም አት​ደ​ነቅ።
12እር​ስዋ የተ​ጠማ ሰው ከቀ​ረ​በው ውኃ ሁሉ እየ​ላሰ እን​ደ​ሚ​ጠጣ፥
በዛ​ፍም ሁሉ ሥር እን​ደ​ሚ​ያ​ርፍ፥#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የተ​ጠማ መን​ገ​ደኛ ምንጭ ባገኘ ጊዜ ከቀ​ረ​በው ውኃ ሁሉ እን​ደ​ሚ​ጠጣ፥ አፍ​ዋን ትከ​ፍ​ታ​ለች ፤ በዛ​ፉም ሥር ሁሉ ትቀ​መ​ጣ​ለች ፤ በፍ​ላ​ጻ​ውም አቅ​ጣጫ ሁሉ ሰገ​ባ​ዋን ትከ​ፍ​ታ​ለች ፤” ይላል።
13ፍላ​ጻ​ው​ንም ከሰ​ገ​ባው እን​ደ​ሚ​ያ​ወጣ ናትና።
የደግ ሴት በረ​ከት
14የሴት ሞገ​ስዋ ባሏን ደስ ያሰ​ኛል።
15ጥበ​ቧም አጥ​ን​ቱን ያለ​መ​ል​መ​ዋል።
16የዋህ ሴት የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስጦታ ናት።
17ለብ​ልህ ሴት ለውጥ የላ​ትም።
18የም​ታ​ፍር ሴት በበ​ረ​ከት ላይ በረ​ከት ናት።
19ለት​ዕ​ግ​ሥ​ተኛ ሴት ለውጥ የላ​ትም።
20ፀሐይ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰማይ እን​ደ​ሚ​ያ​በራ፥
እን​ደ​ዚሁ የደግ ሴት ውበቷ ባማረ በቤቷ ውስጥ ነው።
21የተ​ቀ​ደ​ሰ​ችው መብ​ራት በመ​ቅ​ረዟ ላይ እን​ደ​ም​ታ​በራ፥
እን​ዲሁ የብ​ልህ ሰው የመ​ልኩ ውበት በጠ​ባዩ ውበት ነው።
22በብር ስክ​ተት ላይ እን​ደ​ቆሙ የወ​ርቅ ምሰ​ሶ​ዎች፥
በበጎ ሥራ የቆመ የደግ ሰው እግር አገ​ባ​ብም እን​ዲሁ ነው።
23በእ​ነ​ዚህ በሦ​ስቱ#ግሪኩ “በእ​ነ​ዚህ በሁ​ለቱ” ይላል። ነገ​ሮች ልቡ​ናዬ አዘ​ነ​ብኝ።
24ዐራ​ተ​ኛው#ግሪኩ “ሦስ​ተ​ኛው” ይላል። ግን ብስ​ጭ​ትን አመ​ጣ​ብኝ።
25እነ​ዚ​ህም አር​በ​ኛና ደፋር ሰው አጥቶ ሲቸ​ገር፥
26ጠቢ​ባን ሰዎች ሲስቱ፥
27ጽድ​ቅን ትቶ ወደ ኀጢ​አት የሚ​መ​ለስ ሰው ናቸው።
28እን​ዲህ ያለ​ውን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በጦር ያጠ​ፋ​ዋል።
29አጣሪ ከኀ​ጢ​አቱ በጭ​ንቅ ይድ​ናል፤
መሸ​ተ​ኛም ከበ​ደል ተመ​ልሶ አይ​ጸ​ድ​ቅም።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ