መጽ​ሐፈ ሲራክ 12

12
1በጎ ሥራ በሠ​ራህ ጊዜ የበ​ጎ​ነ​ት​ህን ዋጋ ታገኝ ዘንድ፥
በጎ ሥራ የም​ት​ሠ​ራ​ለ​ትን ዕወቅ።
2ለጻ​ድቅ በጎ አድ​ርግ፥ ዋጋ​ህ​ንም ታገ​ኛ​ለህ፤
በእ​ርሱ ዘንድ ባታ​ገ​ኘው በፈ​ጣ​ሪው ዘንድ ታገ​ኛ​ለህ።
3ኀጢ​አ​ትን በሚ​ሠ​ራና ምጽ​ዋ​ትን በማ​ይ​መ​ጸ​ውት ዘንድ፥
በጎ ሥራ የለም።
4ኀጢ​አ​ተኛ እን​ዳ​ይ​ወ​ስ​ድ​ብህ ለጻ​ድቁ ስጥ።
5ለድሃ መል​ካም አድ​ርግ፥ ለክፉ ግን አት​ስጥ፤
እርሱ እን​ዳ​ይ​ወ​ስ​ድ​ብ​ህና በገ​ን​ዘ​ብህ ድል እን​ዳ​ያ​ደ​ር​ግህ እን​ጀ​ራ​ህን ከል​ክ​ለው፥
በጎ ነገር ስላ​ደ​ረ​ግ​ህ​ለት ፋንታ በእ​ርሱ ዘንድ ክፋ​ትን እጥፍ ሆና ታገ​ኛ​ታ​ለ​ህና።
6እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ኀጢ​አ​ተ​ኞች ሰዎ​ችን ይጠ​ላ​ቸ​ዋ​ልና፤
ክፉ ሰዎ​ች​ንም ይበ​ቀ​ላ​ቸ​ዋ​ልና።
7ለኀ​ጢ​አ​ተኛ ከም​ት​ሰጥ ለጻ​ድቅ ስጥ፤
በደ​ስ​ታም ጊዜ ወዳ​ጅህ አያ​ም​ል​ጥህ።
8በመ​ከ​ራ​ህም ጊዜ ጠላ​ትህ አይ​ሰ​ወ​ርህ።
9ደስ​ታህ ጠላ​ቶ​ች​ህን ያሳ​ዝ​ና​ቸ​ዋል፤
ችግ​ር​ህም ወዳ​ጆ​ች​ህን አስ​ወ​ጥቶ ይሰ​ድ​ዳ​ቸ​ዋል።
10የል​ቡ​ናው ክፋት እንደ ብረት ዝገት ነውና፤
ጠላ​ት​ህን ፈጽ​መህ አት​መ​ነው።
11በተ​ቸ​ገ​ር​ህም ጊዜ እያ​መ​ሰ​ገነ ያገ​ለ​ግ​ል​ሃል፤
ሰው​ነ​ት​ህን አጽ​ናት፤ ከእ​ር​ሱም ተጠ​በቅ፤
እን​ደ​ዛገ መስ​ታ​ወት ትሆ​ን​በ​ታ​ለህ፤ ፈጽ​ሞም አይ​ች​ል​ህም።
12እን​ዳ​ይ​ጎ​ዳህ ባጠ​ገ​ብህ አታ​ቁ​መው፥ በቦ​ታ​ህም አይ​ቀ​መጥ፤
ሹመ​ት​ህ​ንም እን​ዳ​ይ​ወ​ስ​ድ​ብህ በቀ​ኝህ አታ​ስ​ቀ​ም​ጠው።
በመ​ጨ​ረ​ሻም ቃሌን ታው​ቀው ዘንድ አለህ፥ ምክ​ሬ​ንም ታስ​በ​ዋ​ለህ።
13በእ​ባብ ለተ​ነ​ደፈ አስ​ማ​ተኛ፥
ወደ ክፉ አው​ሬም ለቀ​ረበ ሁሉ ማን ያዝ​ን​ለ​ታል?
14ከኀ​ጢ​አ​ተ​ኛም ሰው ጋር የሚ​ሄድ፥
በኀ​ጢ​አ​ቱም የሚ​ተ​ባ​በር እን​ዲሁ ነው።
15ጠላ​ትህ ከአ​ንተ ጋር አንድ ጊዜ ይቆ​ማል፥
ነገር ግን እስ​ክ​ት​መ​ለስ ድረስ#ግሪኩ “በተ​ቸ​ገ​ርህ ጊዜ ግን” ይላል። አታ​የ​ውም፥ ከአ​ን​ተም ጋር አይ​ታ​ገ​ሥም።
16ጠላ​ትህ በከ​ን​ፈሩ ቃሉን ያጣ​ፍ​ጥ​ል​ሃል፥
በልቡ ግን በጕ​ድ​ጓድ ውስጥ ይጥ​ልህ ዘንድ ይመ​ክ​ራል።
ጠላ​ትህ በዐ​ይኑ ያለ​ቅ​ስ​ል​ሃል፥ ካሳ​ተህ በኋላ ግን#ግሪኩ “ጊዜ ከአ​ጋ​ጠ​መው ግን” ይላል። ከደ​ምህ አይ​ጠ​ግ​ብም።
17ብት​ቸ​ገ​ርም ከሁሉ አስ​ቀ​ድሞ በፊ​ትህ ታገ​ኘ​ዋ​ለህ፤
እን​ደ​ሚ​ረ​ዳ​ህም ከጫ​ማህ በታች ራሱን ዝቅ ያደ​ር​ጋል።
18በእጁ ያጨ​በ​ጭ​ባል፤ ራሱ​ንም ይነ​ቀ​ን​ቃል፤
ከዚህ በኋላ ግን ፊቱን መልሶ ይጠ​ቃ​ቀ​ስ​ብ​ሃል።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ