ወደ ሮሜ ሰዎች 7:14-24

ወደ ሮሜ ሰዎች 7:14-24 አማ2000

የኦ​ሪት ሕግ መን​ፈ​ሳዊ እንደ ሆነ እና​ው​ቃ​ለን፤ እኔ ግን ለኀ​ጢ​አት የተ​ሸ​ጥሁ ሥጋዊ ነኝ። የማ​ደ​ር​ገ​ውን አላ​ው​ቅ​ምና፤ የም​ወ​ደ​ው​ንም ያን ምንም አላ​ደ​ር​ገ​ው​ምና፤ ያንኑ የም​ጠ​ላ​ውን ብቻ እሠ​ራ​ለሁ እንጂ። የማ​ል​ወ​ደ​ውን የም​ሠራ ከሆ​ንሁ ግን ያ የኦ​ሪት ሕግ መሠ​ራት ለበጎ እንደ ሆነ ምስ​ክሩ እኔ ነኝ። እን​ግ​ዲ​ያስ በእኔ ላይ ያደ​ረች ኀጢ​አት ናት እንጂ፥ ያን የማ​ደ​ር​ገው እኔ አይ​ደ​ለ​ሁም። በእኔ ማለት በሥ​ጋዬ መል​ካም ነገር እን​ደ​ማ​ይ​ኖር አው​ቃ​ለሁ፤ መል​ካም ሥራ ለመ​ሥ​ራት መሻ​ቱስ በእኔ ዘንድ አለ፤ በጎ ምግ​ባር መሥ​ራት ግን የለ​ኝም። ያን የም​ወ​ደ​ው​ንም በጎ ነገር የማ​ደ​ርግ አይ​ደ​ለም፤ ነገር ግን ያን የም​ጠ​ላ​ውን ክፉ​ውን አደ​ር​ጋ​ለሁ። የማ​ል​ወ​ደ​ው​ንስ የም​ሠራ ከሆነ የም​ሠ​ራው እኔ አይ​ደ​ለ​ሁም፤ በእኔ ላይ ያደ​ረች ኀጢ​አት ናት እንጂ። መል​ካም ሥራ እን​ድ​ሠራ የፈ​ቀ​ደ​ል​ኝን ያን ሕግ እርሱ ክፉ ነገር አም​ጥ​ቶ​ብኝ አገ​ኘ​ሁት። በል​ቡ​ናዬ ውስጥ ያለ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕግ መል​ካም ነው። ነገር ግን በሰ​ው​ነቴ ውስጥ ያለ​ውን ሌላ የኀ​ጢ​አት ሕግ እመ​ለ​ከ​ታ​ለሁ፤ በል​ቡ​ና​ዬም ውስጥ ካለው ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕግ ጋር ተሰ​ል​ፈው ተዋጉ፤ በሰ​ው​ነቴ ውስጥ ያለው ያ የኀ​ጢ​አት ሕግም በረ​ታና ወደ እርሱ ማረ​ከኝ። እኔ ምንና ወራዳ ሰው ነኝ፤ ከዚህ ሟች ሰው​ነቴ ማን ባዳ​ነኝ?