ኦሪት ዘሌ​ዋ​ው​ያን 20

20
የሕግ መተ​ላ​ለፍ ቅጣት
1እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሙሴን እን​ዲህ ብሎ ተና​ገ​ረው፦ 2“ደግሞ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ልጆች እን​ዲህ በላ​ቸው፦ ከእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ወይም በእ​ስ​ራ​ኤል ዘንድ ከሚ​ቀ​መጡ እን​ግ​ዶች ማና​ቸ​ውም ሰው ዘሩን ለሞ​ሎክ#ግዕዝ እና ግሪክ ሰባ. ሊ. “ለመ​ል​አክ” ይላል። አገ​ል​ግ​ሎት ቢሰጥ ፈጽሞ ይገ​ደል፤ የሀ​ገሩ ሕዝብ በድ​ን​ጋይ ይው​ገ​ሩት። 3መቅ​ደ​ሴን ያረ​ክስ ዘንድ፥ የቅ​ዱ​ሳ​ኔ​ንም ስም#ዕብ. “የተ​ቀ​ደ​ሰ​ውን ስሜን” ሲል ግሪክ ሰባ. ሊ. “ለእኔ የተ​ቀ​ደ​ሱ​ትን ስም” ይላል። ያጐ​ስ​ቍል ዘንድ ዘሩን ለሞ​ሎክ አገ​ል​ግ​ሎት ሰጥ​ቶ​አ​ልና እኔ በዚያ ሰው ላይ ፊቴን አከ​ብ​ዳ​ለሁ፤ ከሕ​ዝ​ቡም መካ​ከል ለይች አጠ​ፋ​ዋ​ለሁ። 4ዘሩ​ንም ለሞ​ሎክ ሲሰጥ፥ የሀ​ገሩ ሕዝብ ያን ሰው ቸል ቢሉት፥ አይ​ተው እን​ዳ​ላዩ ቢሆኑ፥ ባይ​ገ​ድ​ሉ​ትም፥ እኔ በዚያ ሰውና በቤተ ሰቡ ላይ ፊቴን አከ​ብ​ዳ​ለሁ። 5እር​ሱ​ንና ከሞ​ሎክ#ግዕዙ “ከመ​ላ​እ​ክት ጋር” ይላል። ጋር ያመ​ነ​ዝሩ ዘንድ የሚ​ከ​ተ​ሉ​ትን ሁሉ ከሕ​ዝ​ባ​ቸው መካ​ከል ለይች አጠ​ፋ​ለሁ።
6“እነ​ር​ሱን ተከ​ትሎ ያመ​ነ​ዝር ዘንድ መና​ፍ​ስት ጠሪ​ዎ​ች​ንና ጠን​ቋ​ዮ​ችን የሚ​ከ​ተል ሰው ቢኖር፥ በዚያ ሰው ላይ ፊቴን አከ​ብ​ዳ​ለሁ፤ ከሕ​ዝ​ቡም መካ​ከል ለይች አጠ​ፋ​ዋ​ለሁ። 7እን​ግ​ዲህ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ላ​ካ​ችሁ ቅዱስ ነኝና#ዕብ. “ሰው​ነ​ታ​ች​ሁን ቀድሱ” የሚል ይጨ​ም​ራል። ቅዱ​ሳን ሁኑ። 8ሕጌ​ንና ትእ​ዛ​ዜን ጠብቁ፤ አድ​ር​ጉ​ትም፤ እኔ የም​ቀ​ድ​ሳ​ችሁ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ላ​ካ​ችሁ ነኝና። 9ማና​ቸ​ውም ሰው አባ​ቱን ወይም እና​ቱን ቢሰ​ድብ ፈጽሞ ይገ​ደል፤ አባ​ቱ​ንና እና​ቱን ሰድ​ቦ​አ​ልና በደ​ለኛ ነው።#ዕብ. “ደሙ በራሱ ላይ ነው” ይላል።
10“ማና​ቸ​ውም ሰው ከሌላ ሰው ሚስት ወይም ከባ​ል​ን​ጀ​ራው ሚስት ጋር ቢያ​መ​ነ​ዝር አመ​ን​ዝ​ራ​ውና አመ​ን​ዝ​ራ​ዪቱ ፈጽ​መው ይገ​ደሉ። 11ማና​ቸ​ውም ሰው ከአ​ባቱ ሚስት ጋር ቢተኛ የአ​ባ​ቱን ኀፍ​ረተ ሥጋ ገል​ጦ​አል፤ ሁለ​ቱም ፈጽ​መው ይገ​ደሉ፤ በደ​ለ​ኞች ናቸው።#ዕብ. “ደማ​ቸው በላ​ያ​ቸው ነው” ይላል። 12ማና​ቸ​ውም ሰው ከም​ራቱ ጋር ቢተኛ ሁለቱ ፈጽ​መው ይገ​ደሉ፤ ጸያፍ ነገር አድ​ር​ገ​ዋል፤ በደ​ለ​ኞች ናቸው። 13ማና​ቸ​ውም ሰው ከሴት ጋር እን​ደ​ሚ​ተኛ ከወ​ንድ ጋር ቢተኛ ሁለቱ ጸያፍ ነገር አድ​ር​ገ​ዋል፤ ፈጽ​መው ይገ​ደሉ፤ በደ​ለ​ኞች ናቸው። 14ማና​ቸ​ውም ሰው እና​ቲ​ቱ​ንና ልጂ​ቱን ቢያ​ገባ ኀጢ​አት ነው፤ በመ​ካ​ከ​ላ​ቸው ኀጢ​አት እን​ዳ​ይ​ሆን እር​ሱ​ንና እነ​ር​ሱን#ግእዙ “እር​ሱ​ንና እር​ስ​ዋን” ይላል። በእ​ሳት ያቃ​ጥ​ሉ​አ​ቸው። 15ማና​ቸ​ውም ሰው ከእ​ን​ስሳ ጋር ቢገ​ናኝ ፈጽሞ ይገ​ደል፤ እን​ስ​ሳ​ዪ​ቱ​ንም ግደ​ሉ​አት። 16ማን​ኛ​ዪ​ቱም ሴት ወደ እን​ስሳ ብት​ቀ​ርብ፥ ከእ​ር​ሱም ጋር ብት​ገ​ናኝ፥ ሴቲ​ቱ​ንና እን​ስ​ሳ​ውን ግደሉ፤ ፈጽ​መው ይገ​ደሉ፤ በደ​ለ​ኞች ናቸው።
17“ማና​ቸ​ውም ሰው የአ​ባ​ቱን ልጅ ወይም የእ​ና​ቱን ልጅ እኅ​ቱን ቢያ​ገባ፥ ኀፍ​ረተ ሥጋ​ዋ​ንም ቢያይ፥ እር​ስ​ዋም ኀፍ​ረተ ሥጋ​ውን ብታይ፥ ይህ ጸያፍ ነገር ነው፤ በሕ​ዝ​ባ​ቸ​ውም ልጆች ፊት ይገ​ደሉ፤ የእ​ኅ​ቱን ኀፍ​ረተ ሥጋ ገል​ጦ​አ​ልና ኀጢ​አ​ቱን ይሸ​ከ​ማል። 18ማና​ቸ​ውም ሰው ከባለ ግዳጅ ሴት ጋር ቢተኛ ኀፍ​ረተ ሥጋ​ዋ​ንም ቢገ​ልጥ፥ ፈሳ​ሽ​ዋን ገል​ጦ​አ​ልና፥ እር​ስ​ዋም የደ​ም​ዋን ፈሳሽ ገል​ጣ​ለ​ችና ሁለቱ ከሕ​ዝ​ባ​ቸው መካ​ከል ተለ​ይ​ተው ይጥፉ። 19የአ​ባ​ት​ህን ወይም የእ​ና​ት​ህን እኅት ኀፍ​ረተ ሥጋ አት​ግ​ለጥ፤ ይህን የሚ​ያ​ደ​ርግ የዘ​መ​ድን ኀፍ​ረተ ሥጋ ገል​ጦ​አል፤ ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ውን ይሸ​ከ​ማሉ። 20ሰውም ከቅ​ርብ ዘመዱ#ዕብ. “ከአ​ጎቱ” ይላል። ሚስት ጋር ቢተኛ የቅ​ርብ ዘመ​ዱን ኀፍ​ረተ ሥጋ ገል​ጦ​አል፤ ያለ ልጅ ይሞ​ታሉ። 21ሰውም የወ​ን​ድ​ሙን ሚስት ቢያ​ገባ ርኵ​ሰት ነው፤ የወ​ን​ድ​ሙን ኀፍ​ረተ ሥጋ ገል​ጦ​አል፤ ያለ ልጅም ይሙቱ።
22“እን​ግ​ዲህ ትቀ​መ​ጡ​ባት ዘንድ የማ​ገ​ባ​ችሁ ምድር እን​ዳ​ት​ተ​ፋ​ችሁ ትእ​ዛ​ዜን ሁሉ፥ ፍር​ዴ​ንም ሁሉ ጠብቁ፤ አድ​ር​ጉ​ትም። 23ከፊ​ታ​ችሁ በማ​ወ​ጣ​ቸው ሕዝብ ሕግ አት​ሂዱ፤ ይህን ሁሉ አድ​ር​ገ​ዋ​ልና ተጸ​የ​ፍ​ኋ​ቸው 24ነገር ግን እና​ንተ፦ ምድ​ራ​ቸ​ውን ትወ​ር​ሳ​ላ​ችሁ፤ ትወ​ር​ሱ​አ​ትም ዘንድ ወተ​ትና ማር የም​ታ​ፈ​ስ​ሰ​ውን ምድር እሰ​ጣ​ች​ኋ​ለሁ አል​ኋ​ችሁ፤ እኔ ከአ​ሕ​ዛብ የለ​የ​ኋ​ችሁ አም​ላ​ካ​ችሁ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነኝ። 25እን​ግ​ዲህ በን​ጹ​ሕና በር​ኩስ እን​ስሳ መካ​ከል፥ በን​ጹ​ሕና በር​ኩ​ስም ወፍ መካ​ከል ለየ​ሁ​ላ​ችሁ፤ ርኩ​ሳን ናቸው ብዬ በለ​የ​ኋ​ቸው በእ​ን​ስ​ሳና በወፍ፥ በም​ድ​ርም ተን​ቀ​ሳ​ቃሽ ሁሉ ነፍ​ሳ​ች​ሁን አታ​ር​ክሱ። 26እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቅዱስ ነኝና፥ ለእ​ኔም ትሆኑ ዘንድ ከአ​ሕ​ዛብ ለይ​ቻ​ች​ኋ​ለ​ሁና ቅዱ​ሳን ትሆ​ኑ​ል​ኛ​ላ​ችሁ።
27“ወንድ ወይም ሴት መና​ፍ​ስ​ትን ቢጠሩ፥ ወይም ጠን​ቋ​ዮች ቢሆኑ ፈጽ​መው ይገ​ደሉ፤ በድ​ን​ጋ​ይም ይው​ገ​ሩ​አ​ቸው፤#ዕብ. “ደማ​ቸው በላ​ያ​ቸው ነው” ይላል። በደ​ለ​ኞች ናቸ​ውና።”

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ