ኦሪት ዘሌዋውያን 20
20
የሕግ መተላለፍ ቅጣት
1እግዚአብሔርም ሙሴን እንዲህ ብሎ ተናገረው፦ 2“ደግሞ የእስራኤልን ልጆች እንዲህ በላቸው፦ ከእስራኤል ልጆች ወይም በእስራኤል ዘንድ ከሚቀመጡ እንግዶች ማናቸውም ሰው ዘሩን ለሞሎክ#ግዕዝ እና ግሪክ ሰባ. ሊ. “ለመልአክ” ይላል። አገልግሎት ቢሰጥ ፈጽሞ ይገደል፤ የሀገሩ ሕዝብ በድንጋይ ይውገሩት። 3መቅደሴን ያረክስ ዘንድ፥ የቅዱሳኔንም ስም#ዕብ. “የተቀደሰውን ስሜን” ሲል ግሪክ ሰባ. ሊ. “ለእኔ የተቀደሱትን ስም” ይላል። ያጐስቍል ዘንድ ዘሩን ለሞሎክ አገልግሎት ሰጥቶአልና እኔ በዚያ ሰው ላይ ፊቴን አከብዳለሁ፤ ከሕዝቡም መካከል ለይች አጠፋዋለሁ። 4ዘሩንም ለሞሎክ ሲሰጥ፥ የሀገሩ ሕዝብ ያን ሰው ቸል ቢሉት፥ አይተው እንዳላዩ ቢሆኑ፥ ባይገድሉትም፥ እኔ በዚያ ሰውና በቤተ ሰቡ ላይ ፊቴን አከብዳለሁ። 5እርሱንና ከሞሎክ#ግዕዙ “ከመላእክት ጋር” ይላል። ጋር ያመነዝሩ ዘንድ የሚከተሉትን ሁሉ ከሕዝባቸው መካከል ለይች አጠፋለሁ።
6“እነርሱን ተከትሎ ያመነዝር ዘንድ መናፍስት ጠሪዎችንና ጠንቋዮችን የሚከተል ሰው ቢኖር፥ በዚያ ሰው ላይ ፊቴን አከብዳለሁ፤ ከሕዝቡም መካከል ለይች አጠፋዋለሁ። 7እንግዲህ እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ቅዱስ ነኝና#ዕብ. “ሰውነታችሁን ቀድሱ” የሚል ይጨምራል። ቅዱሳን ሁኑ። 8ሕጌንና ትእዛዜን ጠብቁ፤ አድርጉትም፤ እኔ የምቀድሳችሁ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝና። 9ማናቸውም ሰው አባቱን ወይም እናቱን ቢሰድብ ፈጽሞ ይገደል፤ አባቱንና እናቱን ሰድቦአልና በደለኛ ነው።#ዕብ. “ደሙ በራሱ ላይ ነው” ይላል።
10“ማናቸውም ሰው ከሌላ ሰው ሚስት ወይም ከባልንጀራው ሚስት ጋር ቢያመነዝር አመንዝራውና አመንዝራዪቱ ፈጽመው ይገደሉ። 11ማናቸውም ሰው ከአባቱ ሚስት ጋር ቢተኛ የአባቱን ኀፍረተ ሥጋ ገልጦአል፤ ሁለቱም ፈጽመው ይገደሉ፤ በደለኞች ናቸው።#ዕብ. “ደማቸው በላያቸው ነው” ይላል። 12ማናቸውም ሰው ከምራቱ ጋር ቢተኛ ሁለቱ ፈጽመው ይገደሉ፤ ጸያፍ ነገር አድርገዋል፤ በደለኞች ናቸው። 13ማናቸውም ሰው ከሴት ጋር እንደሚተኛ ከወንድ ጋር ቢተኛ ሁለቱ ጸያፍ ነገር አድርገዋል፤ ፈጽመው ይገደሉ፤ በደለኞች ናቸው። 14ማናቸውም ሰው እናቲቱንና ልጂቱን ቢያገባ ኀጢአት ነው፤ በመካከላቸው ኀጢአት እንዳይሆን እርሱንና እነርሱን#ግእዙ “እርሱንና እርስዋን” ይላል። በእሳት ያቃጥሉአቸው። 15ማናቸውም ሰው ከእንስሳ ጋር ቢገናኝ ፈጽሞ ይገደል፤ እንስሳዪቱንም ግደሉአት። 16ማንኛዪቱም ሴት ወደ እንስሳ ብትቀርብ፥ ከእርሱም ጋር ብትገናኝ፥ ሴቲቱንና እንስሳውን ግደሉ፤ ፈጽመው ይገደሉ፤ በደለኞች ናቸው።
17“ማናቸውም ሰው የአባቱን ልጅ ወይም የእናቱን ልጅ እኅቱን ቢያገባ፥ ኀፍረተ ሥጋዋንም ቢያይ፥ እርስዋም ኀፍረተ ሥጋውን ብታይ፥ ይህ ጸያፍ ነገር ነው፤ በሕዝባቸውም ልጆች ፊት ይገደሉ፤ የእኅቱን ኀፍረተ ሥጋ ገልጦአልና ኀጢአቱን ይሸከማል። 18ማናቸውም ሰው ከባለ ግዳጅ ሴት ጋር ቢተኛ ኀፍረተ ሥጋዋንም ቢገልጥ፥ ፈሳሽዋን ገልጦአልና፥ እርስዋም የደምዋን ፈሳሽ ገልጣለችና ሁለቱ ከሕዝባቸው መካከል ተለይተው ይጥፉ። 19የአባትህን ወይም የእናትህን እኅት ኀፍረተ ሥጋ አትግለጥ፤ ይህን የሚያደርግ የዘመድን ኀፍረተ ሥጋ ገልጦአል፤ ኀጢአታቸውን ይሸከማሉ። 20ሰውም ከቅርብ ዘመዱ#ዕብ. “ከአጎቱ” ይላል። ሚስት ጋር ቢተኛ የቅርብ ዘመዱን ኀፍረተ ሥጋ ገልጦአል፤ ያለ ልጅ ይሞታሉ። 21ሰውም የወንድሙን ሚስት ቢያገባ ርኵሰት ነው፤ የወንድሙን ኀፍረተ ሥጋ ገልጦአል፤ ያለ ልጅም ይሙቱ።
22“እንግዲህ ትቀመጡባት ዘንድ የማገባችሁ ምድር እንዳትተፋችሁ ትእዛዜን ሁሉ፥ ፍርዴንም ሁሉ ጠብቁ፤ አድርጉትም። 23ከፊታችሁ በማወጣቸው ሕዝብ ሕግ አትሂዱ፤ ይህን ሁሉ አድርገዋልና ተጸየፍኋቸው 24ነገር ግን እናንተ፦ ምድራቸውን ትወርሳላችሁ፤ ትወርሱአትም ዘንድ ወተትና ማር የምታፈስሰውን ምድር እሰጣችኋለሁ አልኋችሁ፤ እኔ ከአሕዛብ የለየኋችሁ አምላካችሁ እግዚአብሔር ነኝ። 25እንግዲህ በንጹሕና በርኩስ እንስሳ መካከል፥ በንጹሕና በርኩስም ወፍ መካከል ለየሁላችሁ፤ ርኩሳን ናቸው ብዬ በለየኋቸው በእንስሳና በወፍ፥ በምድርም ተንቀሳቃሽ ሁሉ ነፍሳችሁን አታርክሱ። 26እኔ እግዚአብሔር ቅዱስ ነኝና፥ ለእኔም ትሆኑ ዘንድ ከአሕዛብ ለይቻችኋለሁና ቅዱሳን ትሆኑልኛላችሁ።
27“ወንድ ወይም ሴት መናፍስትን ቢጠሩ፥ ወይም ጠንቋዮች ቢሆኑ ፈጽመው ይገደሉ፤ በድንጋይም ይውገሩአቸው፤#ዕብ. “ደማቸው በላያቸው ነው” ይላል። በደለኞች ናቸውና።”
Currently Selected:
ኦሪት ዘሌዋውያን 20: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
ኦሪት ዘሌዋውያን 20
20
የሕግ መተላለፍ ቅጣት
1እግዚአብሔርም ሙሴን እንዲህ ብሎ ተናገረው፦ 2“ደግሞ የእስራኤልን ልጆች እንዲህ በላቸው፦ ከእስራኤል ልጆች ወይም በእስራኤል ዘንድ ከሚቀመጡ እንግዶች ማናቸውም ሰው ዘሩን ለሞሎክ#ግዕዝ እና ግሪክ ሰባ. ሊ. “ለመልአክ” ይላል። አገልግሎት ቢሰጥ ፈጽሞ ይገደል፤ የሀገሩ ሕዝብ በድንጋይ ይውገሩት። 3መቅደሴን ያረክስ ዘንድ፥ የቅዱሳኔንም ስም#ዕብ. “የተቀደሰውን ስሜን” ሲል ግሪክ ሰባ. ሊ. “ለእኔ የተቀደሱትን ስም” ይላል። ያጐስቍል ዘንድ ዘሩን ለሞሎክ አገልግሎት ሰጥቶአልና እኔ በዚያ ሰው ላይ ፊቴን አከብዳለሁ፤ ከሕዝቡም መካከል ለይች አጠፋዋለሁ። 4ዘሩንም ለሞሎክ ሲሰጥ፥ የሀገሩ ሕዝብ ያን ሰው ቸል ቢሉት፥ አይተው እንዳላዩ ቢሆኑ፥ ባይገድሉትም፥ እኔ በዚያ ሰውና በቤተ ሰቡ ላይ ፊቴን አከብዳለሁ። 5እርሱንና ከሞሎክ#ግዕዙ “ከመላእክት ጋር” ይላል። ጋር ያመነዝሩ ዘንድ የሚከተሉትን ሁሉ ከሕዝባቸው መካከል ለይች አጠፋለሁ።
6“እነርሱን ተከትሎ ያመነዝር ዘንድ መናፍስት ጠሪዎችንና ጠንቋዮችን የሚከተል ሰው ቢኖር፥ በዚያ ሰው ላይ ፊቴን አከብዳለሁ፤ ከሕዝቡም መካከል ለይች አጠፋዋለሁ። 7እንግዲህ እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ቅዱስ ነኝና#ዕብ. “ሰውነታችሁን ቀድሱ” የሚል ይጨምራል። ቅዱሳን ሁኑ። 8ሕጌንና ትእዛዜን ጠብቁ፤ አድርጉትም፤ እኔ የምቀድሳችሁ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝና። 9ማናቸውም ሰው አባቱን ወይም እናቱን ቢሰድብ ፈጽሞ ይገደል፤ አባቱንና እናቱን ሰድቦአልና በደለኛ ነው።#ዕብ. “ደሙ በራሱ ላይ ነው” ይላል።
10“ማናቸውም ሰው ከሌላ ሰው ሚስት ወይም ከባልንጀራው ሚስት ጋር ቢያመነዝር አመንዝራውና አመንዝራዪቱ ፈጽመው ይገደሉ። 11ማናቸውም ሰው ከአባቱ ሚስት ጋር ቢተኛ የአባቱን ኀፍረተ ሥጋ ገልጦአል፤ ሁለቱም ፈጽመው ይገደሉ፤ በደለኞች ናቸው።#ዕብ. “ደማቸው በላያቸው ነው” ይላል። 12ማናቸውም ሰው ከምራቱ ጋር ቢተኛ ሁለቱ ፈጽመው ይገደሉ፤ ጸያፍ ነገር አድርገዋል፤ በደለኞች ናቸው። 13ማናቸውም ሰው ከሴት ጋር እንደሚተኛ ከወንድ ጋር ቢተኛ ሁለቱ ጸያፍ ነገር አድርገዋል፤ ፈጽመው ይገደሉ፤ በደለኞች ናቸው። 14ማናቸውም ሰው እናቲቱንና ልጂቱን ቢያገባ ኀጢአት ነው፤ በመካከላቸው ኀጢአት እንዳይሆን እርሱንና እነርሱን#ግእዙ “እርሱንና እርስዋን” ይላል። በእሳት ያቃጥሉአቸው። 15ማናቸውም ሰው ከእንስሳ ጋር ቢገናኝ ፈጽሞ ይገደል፤ እንስሳዪቱንም ግደሉአት። 16ማንኛዪቱም ሴት ወደ እንስሳ ብትቀርብ፥ ከእርሱም ጋር ብትገናኝ፥ ሴቲቱንና እንስሳውን ግደሉ፤ ፈጽመው ይገደሉ፤ በደለኞች ናቸው።
17“ማናቸውም ሰው የአባቱን ልጅ ወይም የእናቱን ልጅ እኅቱን ቢያገባ፥ ኀፍረተ ሥጋዋንም ቢያይ፥ እርስዋም ኀፍረተ ሥጋውን ብታይ፥ ይህ ጸያፍ ነገር ነው፤ በሕዝባቸውም ልጆች ፊት ይገደሉ፤ የእኅቱን ኀፍረተ ሥጋ ገልጦአልና ኀጢአቱን ይሸከማል። 18ማናቸውም ሰው ከባለ ግዳጅ ሴት ጋር ቢተኛ ኀፍረተ ሥጋዋንም ቢገልጥ፥ ፈሳሽዋን ገልጦአልና፥ እርስዋም የደምዋን ፈሳሽ ገልጣለችና ሁለቱ ከሕዝባቸው መካከል ተለይተው ይጥፉ። 19የአባትህን ወይም የእናትህን እኅት ኀፍረተ ሥጋ አትግለጥ፤ ይህን የሚያደርግ የዘመድን ኀፍረተ ሥጋ ገልጦአል፤ ኀጢአታቸውን ይሸከማሉ። 20ሰውም ከቅርብ ዘመዱ#ዕብ. “ከአጎቱ” ይላል። ሚስት ጋር ቢተኛ የቅርብ ዘመዱን ኀፍረተ ሥጋ ገልጦአል፤ ያለ ልጅ ይሞታሉ። 21ሰውም የወንድሙን ሚስት ቢያገባ ርኵሰት ነው፤ የወንድሙን ኀፍረተ ሥጋ ገልጦአል፤ ያለ ልጅም ይሙቱ።
22“እንግዲህ ትቀመጡባት ዘንድ የማገባችሁ ምድር እንዳትተፋችሁ ትእዛዜን ሁሉ፥ ፍርዴንም ሁሉ ጠብቁ፤ አድርጉትም። 23ከፊታችሁ በማወጣቸው ሕዝብ ሕግ አትሂዱ፤ ይህን ሁሉ አድርገዋልና ተጸየፍኋቸው 24ነገር ግን እናንተ፦ ምድራቸውን ትወርሳላችሁ፤ ትወርሱአትም ዘንድ ወተትና ማር የምታፈስሰውን ምድር እሰጣችኋለሁ አልኋችሁ፤ እኔ ከአሕዛብ የለየኋችሁ አምላካችሁ እግዚአብሔር ነኝ። 25እንግዲህ በንጹሕና በርኩስ እንስሳ መካከል፥ በንጹሕና በርኩስም ወፍ መካከል ለየሁላችሁ፤ ርኩሳን ናቸው ብዬ በለየኋቸው በእንስሳና በወፍ፥ በምድርም ተንቀሳቃሽ ሁሉ ነፍሳችሁን አታርክሱ። 26እኔ እግዚአብሔር ቅዱስ ነኝና፥ ለእኔም ትሆኑ ዘንድ ከአሕዛብ ለይቻችኋለሁና ቅዱሳን ትሆኑልኛላችሁ።
27“ወንድ ወይም ሴት መናፍስትን ቢጠሩ፥ ወይም ጠንቋዮች ቢሆኑ ፈጽመው ይገደሉ፤ በድንጋይም ይውገሩአቸው፤#ዕብ. “ደማቸው በላያቸው ነው” ይላል። በደለኞች ናቸውና።”