መጽ​ሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ 7:13-15

መጽ​ሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ 7:13-15 አማ2000

ተነ​ሣና ሕዝ​ቡን ቀድስ እን​ዲ​ህም በላ​ቸው፦ ‘እስ​ራ​ኤል ሆይ! እርም የሆነ ነገር በመ​ካ​ከ​ልህ አለ፤ እር​ምም የሆ​ነ​ውን ነገር ከመ​ካ​ከ​ላ​ችሁ እስ​ክ​ታ​ጠፉ ድረስ በጠ​ላ​ቶ​ቻ​ችሁ ፊት መቆም አት​ች​ሉም’ ብሎ የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ተና​ግ​ሮ​አ​ልና እስከ ነገ ራሳ​ች​ሁን አንጹ። ነገም በየ​ነ​ገ​ዳ​ችሁ ትቀ​ር​ባ​ላ​ችሁ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የሚ​ለ​የው ነገድ በየ​ወ​ገ​ኖቹ ይቀ​ር​ባል፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የሚ​ለ​የው ወገን በየ​ቤተ ሰቦቹ ይቀ​ር​ባል፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የሚ​ለ​የው ቤተ ሰብ በየ​ሰዉ ይቀ​ር​ባል። ምል​ክት የታ​የ​በት ሰው የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቃል ኪዳን አፍ​ር​ሶ​አ​ልና፥ በእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ዘንድ በደል አድ​ር​ጎ​አ​ልና፥ እር​ሱና ያለው ሁሉ በእ​ሳት ይቃ​ጠ​ላሉ።”