መጽ​ሐፈ ኢዮብ 26:7-14

መጽ​ሐፈ ኢዮብ 26:7-14 አማ2000

ሰማ​ይን በባዶ ስፍራ ላይ ይዘ​ረ​ጋል፥ ምድ​ሪ​ቱ​ንም አን​ዳች አልባ ያን​ጠ​ለ​ጥ​ላል። ውኃ​ውን በደ​መና ውስጥ ይቋ​ጥ​ራል፥ ደመ​ና​ውም ከታች አይ​ቀ​ደ​ድም። የዙ​ፋ​ኑን ፊት ይከ​ድ​ናል፥ ደመ​ና​ው​ንም ይዘ​ረ​ጋ​በ​ታል። ብር​ሃን ከጨ​ለማ እስ​ከ​ሚ​ለ​ይ​በት ዳርቻ ድረስ፥ የው​ኃ​ውን ፊት በተ​ወ​ሰነ ትእ​ዛዙ ከበ​በው። የሰ​ማይ አዕ​ማድ ይን​ቀ​ጠ​ቀ​ጣሉ፥ ከተ​ግ​ሣ​ጹም የተ​ነሣ ይደ​ነ​ግ​ጣሉ። በኀ​ይሉ ባሕ​ርን ጸጥ ያደ​ር​ጋል፥ በማ​ስ​ተ​ዋ​ሉም ዐን​በ​ሪ​ውን ይገ​ለ​ብ​ጠ​ዋል። የሲ​ኦል በረ​ኞች ለእ​ርሱ አደሉ። በት​እ​ዛ​ዙም ዐመ​ፀ​ኛ​ውን እባብ ገደ​ለው። እነሆ ይህ የመ​ን​ገዱ ክፍል ነው፤ የቀ​ሩ​ት​ንም ነገ​ሮ​ቹን እን​ሰ​ማ​ለን፤ በሚ​ያ​ደ​ር​ግ​በ​ትስ ጊዜ የነ​ጐ​ድ​ጓ​ዱን ኀይል የሚ​ያ​ውቅ ማን ነው?”