ሰማይን በባዶ ስፍራ ላይ ይዘረጋል፥ ምድሪቱንም አንዳች አልባ ያንጠለጥላል። ውኃውን በደመና ውስጥ ይቋጥራል፥ ደመናውም ከታች አይቀደድም። የዙፋኑን ፊት ይከድናል፥ ደመናውንም ይዘረጋበታል። ብርሃን ከጨለማ እስከሚለይበት ዳርቻ ድረስ፥ የውኃውን ፊት በተወሰነ ትእዛዙ ከበበው። የሰማይ አዕማድ ይንቀጠቀጣሉ፥ ከተግሣጹም የተነሣ ይደነግጣሉ። በኀይሉ ባሕርን ጸጥ ያደርጋል፥ በማስተዋሉም ዐንበሪውን ይገለብጠዋል። የሲኦል በረኞች ለእርሱ አደሉ። በትእዛዙም ዐመፀኛውን እባብ ገደለው። እነሆ ይህ የመንገዱ ክፍል ነው፤ የቀሩትንም ነገሮቹን እንሰማለን፤ በሚያደርግበትስ ጊዜ የነጐድጓዱን ኀይል የሚያውቅ ማን ነው?”
መጽሐፈ ኢዮብ 26 ያንብቡ
ያጋሩ
ሁሉንም ሥሪቶች ያነጻጽሩ: መጽሐፈ ኢዮብ 26:7-14
ጥቅሶችን ያስቀምጡ፣ ያለበይነመረብ ያንብቡ፣ አጫጭር የትምህርት ቪዲዮዎችን ይመልከቱ እና ሌሎችም!
ቤት
መጽሐፍ ቅዱስ
እቅዶች
ቪዲዮዎች