መጽሐፈ ኢዮብ 25
25
የበልዳዶስ ንግግር
1አውኬናዊውም በልዳዶስ መለሰ እንዲህም አለ፦
2“ጥንቱን መፈራት በእርሱ ዘንድ ያለ አይደለምን?
በከፍታውም ሁሉን ነገር አድራጊ ነው።#ዕብ. “... ሰላምን አደረገ” ይላል።
3ለሌቦች ዕረፍትን የሚሰጥ እንዳለ የሚመስለው አይኑር።#ዕብ. ልዩነት አለው።
የክፋቱስ ወጥመድ የማይመጣበት ማን ነው?
4ጻድቅ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ሟች” ይላል። ሰው በእግዚአብሔር ፊት እንዴት ንጹሕ ይሆናል?
ከሴትስ የተወለደ ራሱን ንጹሕ ማድረግ እንዴት ይችላል?
5እነሆ፥ ጨረቃ እንኳ ይሰወራል፤ አያበራምም፤#ግሪክ ሰባ. ሊ. “እርሱ ለጨረቃ ትእዛዝ ቢሰጥ አታበራም” ይላል።
ከዋክብትም በፊቱ ንጹሓን አይደሉም።
6ይልቁንስ ፈራሽ የሆነ ሰው፥
ትልም የሆነ የሰው ልጅ ምንኛ ያንስ!”
Currently Selected:
መጽሐፈ ኢዮብ 25: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
መጽሐፈ ኢዮብ 25
25
የበልዳዶስ ንግግር
1አውኬናዊውም በልዳዶስ መለሰ እንዲህም አለ፦
2“ጥንቱን መፈራት በእርሱ ዘንድ ያለ አይደለምን?
በከፍታውም ሁሉን ነገር አድራጊ ነው።#ዕብ. “... ሰላምን አደረገ” ይላል።
3ለሌቦች ዕረፍትን የሚሰጥ እንዳለ የሚመስለው አይኑር።#ዕብ. ልዩነት አለው።
የክፋቱስ ወጥመድ የማይመጣበት ማን ነው?
4ጻድቅ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ሟች” ይላል። ሰው በእግዚአብሔር ፊት እንዴት ንጹሕ ይሆናል?
ከሴትስ የተወለደ ራሱን ንጹሕ ማድረግ እንዴት ይችላል?
5እነሆ፥ ጨረቃ እንኳ ይሰወራል፤ አያበራምም፤#ግሪክ ሰባ. ሊ. “እርሱ ለጨረቃ ትእዛዝ ቢሰጥ አታበራም” ይላል።
ከዋክብትም በፊቱ ንጹሓን አይደሉም።
6ይልቁንስ ፈራሽ የሆነ ሰው፥
ትልም የሆነ የሰው ልጅ ምንኛ ያንስ!”