ትን​ቢተ ኤር​ም​ያስ 31:1-22

ትን​ቢተ ኤር​ም​ያስ 31:1-22 አማ2000

በዚያ ዘመን ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር፤ ለእ​ስ​ራ​ኤል ወገ​ኖች ሁሉ አም​ላክ እሆ​ና​ቸ​ዋ​ለሁ፤ እነ​ር​ሱም ሕዝብ ይሆ​ኑ​ኛል። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፥ “ከሰ​ይፍ የተ​ረ​ፈው ሕዝብ በም​ድረ በዳ ሞገስ አገኘ። ሂዱ፦ እስ​ራ​ኤ​ል​ንም አታ​ጥፉ።” እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ከሩቅ ተገ​ለ​ጠ​ልኝ፤ እን​ዲ​ህም አለኝ፥ “በዘ​ለ​ዓ​ለም ፍቅር ወድ​ጄ​ሃ​ለሁ፤ ስለ​ዚህ በቸ​ር​ነት ሳብ​ሁህ። የእ​ስ​ራ​ኤል ድን​ግል ሆይ እንደ ገና እሠ​ራ​ሻ​ለሁ፤ አን​ቺም ትሠ​ሪ​ያ​ለሽ፤ እንደ ገናም ከበ​ሮ​ሽን አን​ሥ​ተሽ ከዘ​ፋ​ኞች ጋር ትወ​ጫ​ለሽ። እንደ ገናም በሰ​ማ​ርያ ተራ​ሮች ላይ የወ​ይን ተክ​ሎ​ችን ትተ​ክ​ሊ​አ​ለሽ፤ የም​ት​ተ​ክሉ ትከሉ፤ አመ​ስ​ግ​ኑም፤ በኤ​ፍ​ሬም ተራ​ሮች ላይ የሚ​ከ​ራ​ከሩ፦ ተነሡ፤ ወደ ጽዮን ወደ አም​ላ​ካ​ችን ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ውጣ ብለው የሚ​ጠ​ሩ​ባት ቀን ትመ​ጣ​ለ​ችና።” እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላ​ልና፥ “የያ​ዕ​ቆብ ቤት ሆይ! ደስ ይበ​ላ​ችሁ፤ በአ​ሕ​ዛ​ብም አለ​ቆች ላይ እልል በሉ፤ አውሩ፤ አመ​ስ​ግ​ኑም፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሕዝ​ቡን የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ቅሬታ አድ​ኖ​አል በሉ። እነሆ፥ ከሰ​ሜን ሀገር አመ​ጣ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ ከም​ድ​ርም ዳርቻ ለበ​ዓለ ፋሲካ እሰ​በ​ስ​ባ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ ብዙ አሕ​ዛ​ብም ይወ​ለ​ዳሉ፤ ወደ​ዚ​ህም ይመ​ለ​ሳሉ። እያ​ለ​ቀሱ ሄዱ፤ እኔም በማ​ጽ​ና​ናት አመ​ጣ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ በወ​ንዝ ዳር በቅን መን​ገድ አስ​ሄ​ዳ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ በእ​ር​ሱም አይ​ሰ​ና​ከ​ሉም፤ እኔ ለእ​ስ​ራ​ኤል አባት ነኝና፥ ኤፍ​ሬ​ምም በኵሬ ነውና።” አሕ​ዛብ ሆይ! የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቃል ስሙ፤ በሩ​ቅም ላሉ ደሴ​ቶች አው​ሩና፥ “እስ​ራ​ኤ​ልን የበ​ተነ እርሱ ይሰ​በ​ስ​በ​ዋል፤ እረ​ኛም መን​ጋ​ውን እን​ደ​ሚ​ጠ​ብቅ ይጠ​ብ​ቀ​ዋል በሉ። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያዕ​ቆ​ብን ተቤ​ዥ​ቶ​ታል፤ ከበ​ረ​ቱ​በ​ትም እጅ አድ​ኖ​ታል። ይመ​ጣሉ፤ በጽ​ዮ​ንም ተራራ ደስ ይላ​ቸ​ዋል፤ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በጎ​ነት፥ ወደ እህ​ልና ወደ ወይን ጠጅ፥ ወደ ዘይ​ትም፥ ወደ በጎ​ችና ወደ ላሞች ሀገ​ርም ይሰ​በ​ሰ​ባሉ፤ ነፍ​ሳ​ቸ​ውም እንደ ረካች ገነት ትሆ​ና​ለች፤ ከእ​ን​ግ​ዲ​ህም ወዲህ አይ​ራ​ቡም። በዚ​ያን ጊዜም ደና​ግሉ በዘ​ፈን ደስ ይላ​ቸ​ዋል፤ ጐበ​ዛ​ዝ​ቱና ሽማ​ግ​ሌ​ዎ​ቹም በአ​ንድ ላይ ደስ ይላ​ቸ​ዋል፤ እኔም ልቅ​ሶ​አ​ቸ​ውን ወደ ደስታ እመ​ል​ሳ​ለሁ፤ ከኀ​ዘ​ና​ቸ​ውም ደስ አሰ​ኛ​ቸ​ዋ​ለሁ። የካ​ህ​ና​ቱ​ንም የሌ​ዊን ልጆች ሰው​ነት ከፍ ከፍ አደ​ር​ጋ​ታ​ለሁ፤ አረ​ካ​ታ​ለሁ፤ ሕዝ​ቤም ከበ​ረ​ከቴ ይጠ​ግ​ባል፥” ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፥ “የኀ​ዘን፥ የል​ቅ​ሶና የጩ​ኸት ድምፅ በራማ ተሰማ፤ ራሔል ስለ ልጆ​ችዋ አለ​ቀ​ሰች፤ የሉ​ምና ስለ ልጆ​ችዋ መጽ​ና​ና​ትን እንቢ አለች። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ ድም​ፅ​ሽን ከል​ቅሶ፥ ዐይ​ኖ​ች​ሽ​ንም ከእ​ንባ ከል​ክዪ፤ ለሥ​ራሽ ዋጋ ይሆ​ና​ልና፥ ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር፤ ከጠ​ላ​ትም ምድር ይመ​ለ​ሳሉ። ለፍ​ጻ​ሜ​ሽም ተስፋ አለ፥ ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር፥ ልጆ​ች​ሽም ወደ ሀገ​ራ​ቸው ይመ​ለ​ሳሉ። “ኤፍ​ሬም ሲጨ​ነቅ መስ​ማ​ትን ሰማሁ፤ እን​ዲ​ህም አለ፦ ቀጣ​ኸኝ እኔም እን​ዳ​ል​ቀና ወይ​ፈን ተቀ​ጣሁ፤ አንተ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ላኬ ነህና መል​ሰኝ፤ እኔም እመ​ለ​ሳ​ለሁ። ከተ​መ​ለ​ስሁ በኋላ ተጸ​ጸ​ትሁ፤ ከተ​ገ​ሠ​ጽ​ሁም በኋላ ጭኔን ጸፋሁ፤ የብ​ላ​ቴ​ን​ነ​ቴ​ንም ስድብ ተሸ​ክ​ሜ​አ​ለ​ሁና አፈ​ርሁ፥ ተዋ​ረ​ድ​ሁም። በእ​ው​ነት ኤፍ​ሬም ለእኔ የተ​ወ​ደደ ልጅ ነው፤ ደስ የሚ​ያ​ሰ​ኝም ሕፃን ነው፤ በእ​ርሱ ላይ በተ​ና​ገ​ርሁ ቍጥር አስ​በ​ዋ​ለሁ፤ ስለ​ዚህ አን​ጀቴ ታወ​ከ​ች​ለት፤ ርኅ​ራ​ኄም እራ​ራ​ለ​ታ​ለሁ፥” ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር። “ለራ​ስሽ የመ​ን​ገድ ምል​ክት አድ​ርጊ፥ መን​ገ​ድ​ንም የሚ​መሩ ዐም​ዶ​ችን ትከዪ፤ ልብ​ሽ​ንም ወደ ሄድ​ሽ​በት መን​ገድ ወደ ጥር​ጊ​ያው አቅኚ፤ አንቺ የእ​ስ​ራ​ኤል ድን​ግል ሆይ! ተመ​ለሺ፤ ወደ እነ​ዚ​ህም ወደ ከተ​ሞ​ችሽ እያ​ለ​ቀ​ስሽ ተመ​ለሺ። አንቺ ከዳ​ተኛ ልጅ ሆይ! እስከ መቼ ትቅ​በ​ዘ​በ​ዣ​ለሽ? እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በም​ድር ላይ አዲስ ነገር ፈጥ​ሮ​አ​ልና ሰው ወደ ድኅ​ነት ይመ​ጣል።”