መጽ​ሐፈ ዕዝራ 6:13-22

መጽ​ሐፈ ዕዝራ 6:13-22 አማ2000

ንጉ​ሡም ዳር​ዮስ እንደ ላከው ቃል፥ በዚ​ያን ጊዜ በወ​ንዝ ማዶ ያለ ገዥ ተን​ት​ናይ ደግሞ አስ​ተ​ር​ቡ​ዝ​ናይ ተባ​ባ​ሪ​ዎ​ቻ​ቸ​ውም እን​ዲሁ ተግ​ተው አደ​ረጉ። የአ​ይ​ሁድ ሽማ​ግ​ሌ​ዎ​ችና ሌዋ​ው​ያ​ንም በነ​ቢዩ በሐ​ጌና በአዶ ልጅ በዘ​ካ​ር​ያስ ትን​ቢት መሠ​ረት ሠሩ፤ ተከ​ና​ወ​ነ​ላ​ቸ​ውም። እንደ እስ​ራ​ኤ​ልም አም​ላክ ትእ​ዛዝ፥ እንደ ፋር​ስም ነገ​ሥ​ታት እንደ ቂሮ​ስና እንደ ዳር​ዮስ፥ እንደ አር​ተ​ሰ​ስ​ታም ትእ​ዛዝ ሠር​ተው ፈጸሙ። ይህም ቤት በን​ጉሡ በዳ​ር​ዮስ መን​ግ​ሥት በስ​ድ​ስ​ተ​ኛው ዓመት አዳር በሚ​ባል ወር በሦ​ስ​ተ​ኛው ቀን ተፈ​ጸመ። የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ካህ​ና​ቱና ሌዋ​ው​ያኑ፥ የቀ​ሩ​ትም የም​ር​ኮ​ኞች ልጆች የዚ​ህን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ቅዳሴ በደ​ስታ አደ​ረጉ። በዚ​ህም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ቅዳሴ መቶ ወይ​ፈ​ኖ​ችና ሁለት መቶ አውራ በጎች፥ አራት መቶም የበግ ጠቦ​ቶች አቀ​ረቡ፤ ስለ ኀጢ​አ​ትም መሥ​ዋ​ዕት እንደ እስ​ራ​ኤል ነገ​ዶች ቍጥር ለእ​ስ​ራ​ኤል ሁሉ ዐሥራ ሁለት አውራ ፍየ​ሎች አቀ​ረቡ። በሙ​ሴም መጽ​ሐፍ እንደ ተጻ​ፈው በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ባለው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አገ​ል​ግ​ሎት ላይ ካህ​ና​ቱን በየ​ማ​ዕ​ር​ጋ​ቸው፥ ሌዋ​ው​ያ​ኑ​ንም በየ​ክ​ፍ​ላ​ቸው አቆሙ። የም​ር​ኮ​ኞ​ቹም ልጆች በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ወር በዐ​ሥራ አራ​ተ​ኛው ቀን ፋሲ​ካ​ውን አደ​ረጉ። ካህ​ና​ቱና ሌዋ​ው​ያ​ኑም አንድ ሆነው ነጽ​ተው ነበር፤ ሁሉም ንጹ​ሓን ነበሩ፤ ለም​ር​ኮ​ኞ​ቹም ልጆች ሁሉ፥ ለወ​ን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው ለካ​ህ​ናቱ፥ ለራ​ሳ​ቸ​ውም የፋ​ሲ​ካ​ውን በግ ዐረዱ። ከም​ር​ኮም ተመ​ል​ሰው የመ​ጡት የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች፥ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ይፈ​ልጉ ዘንድ ራሳ​ቸ​ውን ከም​ድር አሕ​ዛብ ርኵ​ሰት ለይ​ተው ወደ እነ​ርሱ መጥ​ተው የነ​በ​ሩት ሁሉ ፋሲ​ካ​ውን በሉ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ደስ አሰ​ኝ​ቶ​አ​ቸ​ዋ​ልና፥ የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም አም​ላክ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ለመ​ሥ​ራት እጃ​ቸ​ውን ያጸና ዘንድ የአ​ሦ​ርን ንጉሥ ልብ ወደ እነ​ርሱ መል​ሶ​አ​ልና የቂ​ጣ​ውን በዓል ሰባት ቀን በደ​ስታ አደ​ረጉ።