መጽ​ሐፈ ዕዝራ 2

2
ወደ ሀገ​ራ​ቸው የተ​መ​ለሱ የአ​ይ​ሁድ ስም ዝር​ዝር
(ነህ. 7፥4-73)
1የባ​ቢ​ሎ​ንም ንጉሥ ናቡ​ከ​ደ​ነ​ፆር ወደ ባቢ​ሎን ከማ​ረ​ካ​ቸው ምር​ኮ​ኞች ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምና ወደ ይሁዳ፥ ወደ እየ​ከ​ተ​ማ​ቸው የተ​መ​ለ​ሱት የሀ​ገር ልጆች እነ​ዚህ ናቸው። 2ከዘ​ሩ​ባ​ቤል፥ ከኢ​ያሱ፥ ከነ​ህ​ምያ፥ ከሠ​ራያ፥ ከሮ​ሃ​ልያ፥ ከመ​ር​ዶ​ክ​ዮስ፥ ከበ​ላ​ሳን፥ ከመ​ሴ​ፋር፥ ከበ​ጎ​ዋይ፥ ከሬ​ሁም፥ ከበ​ዓና ጋር መጡ። የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ሕዝብ ሰዎች ቍጥር ይህ ነው፤ 3የፋ​ሮስ ልጆች ሁለት ሺህ መቶ ሰባ ሁለት። 4የሰ​ፋ​ጥ​ያስ ልጆች ሦስት መቶ ሰባ ሁለት። 5የኤ​ራስ ልጆች ሰባት መቶ ሰባ አም​ስት። 6ከያ​ሱ​ኤና ከዮ​አብ ልጆች የሆ​ኑት የፈ​ሐት ሞዓብ ልጆች ሁለት ሺህ ስም​ንት መቶ ዐሥራ ሁለት። 7የኤ​ላም ልጆች ሺህ ሁለት መቶ አምሳ አራት። 8የዛ​ቱዕ ልጆች ዘጠኝ መቶ አርባ አም​ስት። 9የዘ​ካይ ልጆች ሰባት መቶ ስድሳ። 10የባኒ ልጆች ስድ​ስት መቶ አርባ ሁለት። 11የቢ​ባይ ልጆች ስድ​ስት መቶ ሃያ ሦስት። 12የዓ​ዝ​ጋድ ልጆች ሺህ ሁለት መቶ ሃያ ሁለት። 13የአ​ዶ​ኒ​ቃም ልጆች ስድ​ስት መቶ ስድሳ ስድ​ስት። 14የበ​ጕ​ዋይ ልጆች ሁለት ሺህ አምሳ ስድ​ስት። 15የዓ​ዲን ልጆች አራት መቶ አምሳ አራት። 16ከሕ​ዝ​ቅ​ያስ ወገን የአ​ጤር ልጆች ዘጠና ስም​ንት። 17የቤ​ሳይ ልጆች ሦስት መቶ ሃያ ሦስት። 18የዮራ ልጆች መቶ ዐሥራ ሁለት። 19የሐ​ሱም ልጆች ሁለት መቶ ሃያ ሦስት። 20የጋ​ቤር ልጆች ዘጠና አም​ስት። 21የቤተ ልሔም ልጆች መቶ ሃያ ሦስት። 22የነ​ጦፋ ልጆች አምሳ ስድ​ስት። 23የዓ​ና​ቶት ልጆች መቶ ሃያ ስም​ንት። 24የዓ​ዝ​ሞት ልጆች አርባ ሁለት። 25የቂ​ር​ያ​ት​ይ​ዓ​ሪ​ምና የቃ​ፌር፥ የብ​ኤ​ሮ​ትም ልጆች ሰባት መቶ አርባ ሦስት። 26የራ​ማና የጋ​ባዕ ልጆች ስድ​ስት መቶ ሃያ አንድ። 27የመ​ኪ​ማስ ሰዎች መቶ ሃያ ሁለት። 28የቤ​ቴ​ልና የጋይ ሰዎች ሁለት መቶ ሃያ ሦስት። 29የና​ባው ልጆች አምሳ ሁለት። 30የመ​ጌ​ባስ ልጆች መቶ አምሳ ስድ​ስት። 31የኤ​ላ​ማር ልጆች ሺህ ሁለት መቶ አምሳ አራት። 32የኤ​ላም ልጆች ሦስት መቶ ሃያ። 33የሎድ፥ የሐ​ዲ​ድና የኦ​ኖም ልጆች ሰባት መቶ ሃያ አም​ስት። 34የኢ​ያ​ሪኮ ልጆች ሦስት መቶ አርባ አም​ስት። 35የሴ​ዓ​ናህ ልጆች ሦስት ሺህ ስድ​ስት መቶ ሠላሳ። 36ካህ​ናቱ ከኢ​ያሱ ወገን የዮ​ዳኤ ልጆች ዘጠኝ መቶ ሰባ ሦስት። 37የኢ​ሜር ልጆች ሺህ አምሳ ሁለት። 38የፋ​ስ​ኮር ልጆች ሺህ ሁለት መቶ አርባ ሰባት። 39የኤ​ረም ልጆች ሺህ ዐሥራ ሰባት።#ግሪክ ሰባ. ሊ. “አንድ ሽህ ሰባት” ይላል።
40ሌዋ​ው​ያኑ፤ ከሁ​ድያ ልጆች ወገን የኢ​ዮ​ስ​ስና የቀ​ዳ​ም​ሔል ልጆች ሰባ አራት።
41መዘ​ም​ራኑ የአ​ሳፍ ልጆች መቶ ሃያ ስም​ንት።
42የበ​ረ​ኞች ልጆች፥ የሰ​ሎም ልጆች፥ የአ​ጤር ልጆች፥ የጤ​ል​ሞን ልጆች፥ የዓ​ቁብ ልጆች፥ የሐ​ጢጣ ልጆች፥ የሰ​በ​ዋይ ልጆች ሁሉ መቶ ሠላሳ ዘጠኝ።
43ናታ​ኒም፤ የሲሓ ልጆች፥ የሐ​ሡፊ ልጆች፥ የጠ​ብ​ዖት ልጆች፤ 44የቃ​ዴስ ልጆች፥ የሲ​ሔል ልጆች፥ የፋ​ዶን ልጆች፤ 45የል​ባና ልጆች፥ የአ​ጋባ ልጆች፥ የዓ​ቁብ ልጆች፥ 46የአ​ጋብ ልጆች፥ የሰ​ላሚ ልጆች፥ የሐ​ናን ልጆች፤ 47የጋ​ዱል ልጆች፥ የጋ​ሐር ልጆች፥ የራ​እያ ልጆች፤ 48የረ​አ​ሶን ልጆች፥ የኒ​ቆዳ ልጆች፥ የጋ​ሴም ልጆች፤ 49የዓ​ዝ​ያት ልጆች፥ የፋ​ሒስ ልጆች፥ የባሲ ልጆች፤ 50የአ​ሲና ልጆች፥ የም​ዑ​ና​ው​ያን ልጆች፥ የና​ፌ​ሶን ልጆች፤ 51የበ​ቅ​ቡቅ ልጆች፥ የሐ​ቁፋ ልጆች፥ የሐ​ር​ሑር ልጆች፤ 52የበ​ስ​ሎት ልጆች፥ የማ​ሁድ ልጆች፥ የአ​ሪስ ልጆች፤ 53የበ​ር​ቆስ ልጆች፥ የሲ​ሣራ ልጆች፥ የቴማ ልጆች፥ 54የን​ስያ ልጆች፥ የአ​ጡፋ ልጆች።
55የሰ​ሎ​ሞን አገ​ል​ጋ​ዮች ልጆች፤ የሳጢ ልጆች፥ የሰ​ፌ​ርታ ልጆች፥ የፋ​ዱ​ርሓ ልጆች፤ 56የኢ​ያ​ሔል ልጆች፥ የደ​ር​ቆን ልጆች፥ የጌ​ዴል ልጆች፤ 57የሰ​ፋ​ጥ​ያስ ልጆች፥ የአ​ጤል ልጆች፥ የፎ​ኬ​ርት ልጆች፥ የሐ​ፂ​ባ​ይም ልጆች፥ የአሚ ልጆች። 58እነ​ዚህ ናታ​ኒም ሁሉና የሰ​ሎ​ሞን አገ​ል​ጋ​ዮች ልጆች ሦስት መቶ ዘጠና ሁለት ነበሩ።
59ከቲ​ል​ሜላ፥ ከቴ​ላ​ርሳ፥ ከክ​ሩብ፥ ከሐ​ዳን፥ ከኤ​ሜር የወጡ እነ​ዚህ ነበሩ፤ ነገር ግን የአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን ቤቶ​ችና ዘራ​ቸ​ውን ወይም ከእ​ስ​ራ​ኤል ወገን መሆ​ና​ቸ​ውን ያስ​ታ​ውቁ ዘንድ አል​ቻ​ሉም፤ 60የዳ​ላያ ልጆች፥#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የቡኣ ልጆች” የሚል ይጨ​ም​ራል። የጦ​ብያ ልጆች፥ የኒ​ቆዳ ልጆች፥ ስድ​ስት መቶ አምሳ ሁለት ነበሩ። 61ከካ​ህ​ና​ቱም ልጆች፤ የአ​ብያ ልጆች፥ የአ​ቆስ ልጆች፥ ከገ​ለ​ዓ​ዳ​ዊው ከቤ​ር​ዜሊ ልጆች ሚስት ያገባ፥ በስ​ማ​ቸ​ውም የተ​ጠራ የቤ​ር​ዜሊ ልጆች። 62እነ​ዚህ በት​ው​ልድ መጽ​ሐፍ ትው​ል​ዳ​ቸ​ውን ፈለጉ፤ ነገር ግን አል​ተ​ገ​ኘም፤ ከክ​ህ​ነ​ትም ተከ​ለ​ከሉ። 63ሐቲ​ር​ሰ​ስ​ታም፥ “በኡ​ሪ​ምና በቱ​ሚም የሚ​ፈ​ርድ ካህን እስ​ኪ​ነሣ ድረስ ከቅ​ዱሰ ቅዱ​ሳኑ አት​በ​ሉም” አላ​ቸው።
64ጉባ​ኤው ሁሉ አርባ ሁለት ሺህ ሦስት መቶ ስድሳ ነበሩ። 65ይኸ​ውም ሰባት ሺህ ሦስት መቶ ሠላሳ ሰባት ከነ​በሩ ከሎ​ሌ​ዎ​ቻ​ቸ​ውና ከገ​ረ​ዶ​ቻ​ቸው ሌላ ሁለት መቶ ወን​ዶች መዘ​ም​ራ​ንና ሴቶች መዘ​ም​ራ​ትም ነበ​ሩ​አ​ቸው። 66ፈረ​ሶ​ቻ​ቸ​ውም ሰባት መቶ ሠላሳ ስድ​ስት፥ በቅ​ሎ​ዎ​ቻ​ቸ​ውም ሁለት መቶ አርባ አም​ስት፥ 67ግመ​ሎ​ቻ​ቸ​ውም አራት መቶ ሠላሳ አም​ስት፥ አህ​ዮ​ቻ​ቸ​ውም ስድ​ስት ሺህ ሰባት መቶ ሃያ ነበሩ።
68በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ወዳ​ለው ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት በመጡ ጊዜ ከአ​ባ​ቶች ቤቶች አለ​ቆች አያ​ሌ​ዎች ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት በስ​ፍ​ራው ይሠ​ሩት ዘንድ በፈ​ቃ​ዳ​ቸው ሰጡ። 69ስድሳ አንድ ሺህም የወ​ርቅ ዳሪክ፥ አም​ስት ሺህም ምናን ብር፥ አንድ መቶም የካ​ህ​ናት ልብስ እንደ ችሎ​ታ​ቸው ወደ ሥራው ቤተ መዛ​ግ​ብት አቀ​ረቡ።
70ካህ​ና​ቱና ሌዋ​ው​ያ​ኑም፥ ከሕ​ዝ​ቡም አያ​ሌ​ዎች፥ መዘ​ም​ራ​ኑና በረ​ኞ​ቹም፥ ናታ​ኒ​ምም በከ​ተ​ሞ​ቻ​ቸው፥ እስ​ራ​ኤ​ልም ሁሉ በከ​ተ​ሞ​ቻ​ቸው ተቀ​መጡ።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ