መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊ 27
27
1የእስራኤልም ልጆች የአባቶች ቤቶች አለቆችና የሺህ አለቆች፥ የመቶ አለቆችም ለንጉሡና ለንጉሡ ትእዛዝ ሁሉ የሚያገለግሉ ሹማምት እንደ ቍጥራቸው በየክፍላቸው እነዚህ ነበሩ። እነዚህም ክፍሎች እያንዳንዳቸው ሃያ አራት ሺህ ሆነው በዓመቱ ወራት ሁሉ በየወሩ ይገቡና ይወጡ ነበር። 2ለመጀመሪያው ወር በአንደኛው ክፍል ላይ የዘብድኤል ልጅ ያሶብአም ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ። 3እርሱም ከፋሬስ ልጆች ነበረ፤ ለመጀመሪያው ወር በጭፍራ አለቆች ሁሉ ላይ ተሾሞ ነበር። 4በሁለተኛውም ወር ክፍል ላይ የኤቲ ልጅ ዶድያ ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሚኮሎት አለቃ ነበር፤#“በእርሱ ክፍል ሚኮሎት አለቃ ነበረ” በዕብ. እና በአንዳንድ የግእዝ ዘርዕ የለም። በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ። 5በሦስተኛው ወር ሦስተኛው የጭፍራ አለቃ የካህኑ የዮዳሄ ልጅ በናያስ ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሽህ ጭፍራ ነበረ። 6ይህ በናያስ ከሠላሳው መካከል ኀያል ሆኖ በሠላሳው ላይ ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ልጁ ዓሚዛባድ ነበረ። 7በአራተኛው ወር አራተኛው አለቃ የኢዮአብ ወንድም አሳሄል ነበረ፤ ከእርሱም በኋላ ልጁ ዝባድያና ወንድሞቹ ነበሩ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ። 8በአምስተኛው ወር አምስተኛው አለቃ ይዝራዊው ሰማኦት ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ። 9በስድስተኛውም ወር ስድስተኛው አለቃ የቴቁሓዊው የአቂስ ልጅ ኢይዝራኤል ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ። 10በሰባተኛውም ወር ሰባተኛው አለቃ ከኤፍሬም ልጆች የሆነ ፍሎሳዊው ከሊስ ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ። 11በስምንተኛው ወር ስምንተኛው አለቃ ከዛራውያን የነበረው ኩሳታዊው ሲቦካይ ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ። 12በዘጠነኛው ወር ዘጠነኛው አለቃ ከብንያማውያን የነበረው ዓናቶታዊው አቢዔዜር ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ። 13በዐሥረኛው ወር ዐሥረኛው አለቃ ከዛራውያን የነበረው ነጦፋዊው መዐርኢ ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ። 14በዐሥራ አንደኛው ወር ዐሥራ አንደኛው አለቃ ከኤፍሬም ልጆች የነበረው ፍርዓቶናዊው በናያስ ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ። 15በዐሥራ ሁለተኛው ወር ዐሥራ ሁለተኛው አለቃ ከጎቶንያል ወገን የነበረው ነጦፋታዊው ኬልዳይ ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ።
16በእስራኤልም ነገዶች ላይ እነዚህ ነበሩ፦ በሮቤላውያን ላይ የዝክሪ ልጅ ኤልያዛር አለቃ ነበረ፤ በስምዖናውያን ልጅ የመዓካ ልጅ ሰፋጥያስ ነበረ፤ 17በሌዊ ወገን ላይ የቀሙኤል ልጅ አሰብያ፤ በአሮን ወገን ላይ ሳዶቅ፤ 18በይሁዳ ወገን ላይ ከዳዊት ወንድሞች ኤልያብ፤ በይሳኮር ወገን ላይ የሚካኤል ልጅ ዖምሪ፤ 19በዛብሎን ወገን ላይ የአብድዩ ልጅ ሶማዒያስ፤ በንፍታሌም ወገን ላይ የዖዜሄል ልጅ ኢያሪሙት፤ 20በኤፍሬም ልጆች ላይ የአዛዝያ ልጅ ሆሴዕ፤ በምናሴ ነገድ እኩሌታ ላይ የፈዳያ ልጅ ኢዩኤል፤ 21በገለዓድ ምድር ባለው በምናሴ ነገድ እኩሌታ ላይ የዘብድያስ ልጅ ኢዮዳኢ፤ በብንያምም ልጆች ላይ የአበኔር ልጅ አሳሄል፤ 22በዳን ወገንም ላይ የኢዮራም ልጅ ዓዛርኤል፤ እነዚህ የእስራኤል ነገዶች አለቆች ነበሩ። 23ነገር ግን እግዚአብሔር ሕዝቡ እስራኤልን እንደ ሰማይ ከዋክብት ያበዛ ዘንድ ተናግሮ ነበርና ዳዊት ከሃያ ዓመት በታች የነበሩትን አልቈጠረም። 24የሶርህያ ልጅ ኢዮአብም መቍጠር ጀመረ፤ ነገር ግን አልፈጸመም፤ ስለዚህ ነገር በእስራኤል ላይ ቍጣ ሆነ፤ ቍጥራቸውም በንጉሡ በዳዊት የታሪክ መጽሐፍ አልተጻፈም።
25በንጉሡም ቤተ መዛግብት ላይ የዓዳኤል ልጅ ዓዝሞት ሹም ነበረ፤ በሜዳውም፥ በከተሞቹም፥ በመንደሮቹም፥ በግንቦቹም ቤተ መዛግብት ላይ የዖዝያ ልጅ ዮናታን ሹም ነበረ፤ 26መሬቱን በሚያበጃጁትና እርሻውን በሚያርሱት ላይ የክሉብ ልጅ ዔዝሪ ሹም ነበረ፤ 27በወይንም ቦታዎች ላይ ራማታዊው ሰሜኢ ሹም ነበረ፤ ለወይንም ጠጅ ዕቃ ቤት በሚሆነው በወይኑ ሰብል ላይ የሳፍኒው ዘብዲ ሹም ነበረ። 28በቈላውም ውስጥ ባሉት በወይራውና በሾላው ዛፎች ላይ ጌድራዊው በአልሐናን ሹም ነበረ፤ በዘይቱም ቤቶች ላይ ኢዮአስ ሹም ነበረ፤ 29በሳሮንም በሚሰማሩ ከብቶች ላይ ሳሮናዊው ሰጥራይ ሹም ነበረ፤ በሸለቆዎቹም ውስጥ በነበሩት ከብቶች ላይ የዓድላይ ልጅ ሳፋጥ ሹም ነበረ፤ 30በግመሎቹም ላይ እስማኤላዊው ኤቢያስ ሹም ነበረ፤ በአህዮቹም ላይ ሜሮኖታዊው ኢያድስ ሹም ነበረ፤ 31በበጎችም ላይ አጋራዊው ያዚዝ ሹም ነበረ። እነዚህ ሁሉ በንጉሡ በዳዊት ሀብት ላይ ሹሞች ነበሩ።
32አስተዋይና ጸሓፊ የነበረው በአባቱ በኩል የዳዊት አጎት ዮናታን አማካሪ ነበረ፤ የአክማኔም ልጅ ኢያሔኤል ከንጉሡ ልጆች ጋር ነበረ፤ 33አኪጦፌልም የንጉሡ አማካሪ ነበረ። አርካዊው ኩሲም የንጉሡ አንደኛ ወዳጅ ነበረ፤ 34ከአኪጦፌልም ቀጥሎ የበናያስ ልጅ ዮዳሔና አብያታር ነበሩ፤ ኢዮአብም የንጉሡ ሠራዊት አለቃ ነበረ።
Currently Selected:
መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊ 27: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊ 27
27
1የእስራኤልም ልጆች የአባቶች ቤቶች አለቆችና የሺህ አለቆች፥ የመቶ አለቆችም ለንጉሡና ለንጉሡ ትእዛዝ ሁሉ የሚያገለግሉ ሹማምት እንደ ቍጥራቸው በየክፍላቸው እነዚህ ነበሩ። እነዚህም ክፍሎች እያንዳንዳቸው ሃያ አራት ሺህ ሆነው በዓመቱ ወራት ሁሉ በየወሩ ይገቡና ይወጡ ነበር። 2ለመጀመሪያው ወር በአንደኛው ክፍል ላይ የዘብድኤል ልጅ ያሶብአም ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ። 3እርሱም ከፋሬስ ልጆች ነበረ፤ ለመጀመሪያው ወር በጭፍራ አለቆች ሁሉ ላይ ተሾሞ ነበር። 4በሁለተኛውም ወር ክፍል ላይ የኤቲ ልጅ ዶድያ ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሚኮሎት አለቃ ነበር፤#“በእርሱ ክፍል ሚኮሎት አለቃ ነበረ” በዕብ. እና በአንዳንድ የግእዝ ዘርዕ የለም። በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ። 5በሦስተኛው ወር ሦስተኛው የጭፍራ አለቃ የካህኑ የዮዳሄ ልጅ በናያስ ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሽህ ጭፍራ ነበረ። 6ይህ በናያስ ከሠላሳው መካከል ኀያል ሆኖ በሠላሳው ላይ ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ልጁ ዓሚዛባድ ነበረ። 7በአራተኛው ወር አራተኛው አለቃ የኢዮአብ ወንድም አሳሄል ነበረ፤ ከእርሱም በኋላ ልጁ ዝባድያና ወንድሞቹ ነበሩ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ። 8በአምስተኛው ወር አምስተኛው አለቃ ይዝራዊው ሰማኦት ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ። 9በስድስተኛውም ወር ስድስተኛው አለቃ የቴቁሓዊው የአቂስ ልጅ ኢይዝራኤል ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ። 10በሰባተኛውም ወር ሰባተኛው አለቃ ከኤፍሬም ልጆች የሆነ ፍሎሳዊው ከሊስ ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ። 11በስምንተኛው ወር ስምንተኛው አለቃ ከዛራውያን የነበረው ኩሳታዊው ሲቦካይ ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ። 12በዘጠነኛው ወር ዘጠነኛው አለቃ ከብንያማውያን የነበረው ዓናቶታዊው አቢዔዜር ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ። 13በዐሥረኛው ወር ዐሥረኛው አለቃ ከዛራውያን የነበረው ነጦፋዊው መዐርኢ ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ። 14በዐሥራ አንደኛው ወር ዐሥራ አንደኛው አለቃ ከኤፍሬም ልጆች የነበረው ፍርዓቶናዊው በናያስ ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ። 15በዐሥራ ሁለተኛው ወር ዐሥራ ሁለተኛው አለቃ ከጎቶንያል ወገን የነበረው ነጦፋታዊው ኬልዳይ ነበረ፤ በእርሱም ክፍል ሃያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ።
16በእስራኤልም ነገዶች ላይ እነዚህ ነበሩ፦ በሮቤላውያን ላይ የዝክሪ ልጅ ኤልያዛር አለቃ ነበረ፤ በስምዖናውያን ልጅ የመዓካ ልጅ ሰፋጥያስ ነበረ፤ 17በሌዊ ወገን ላይ የቀሙኤል ልጅ አሰብያ፤ በአሮን ወገን ላይ ሳዶቅ፤ 18በይሁዳ ወገን ላይ ከዳዊት ወንድሞች ኤልያብ፤ በይሳኮር ወገን ላይ የሚካኤል ልጅ ዖምሪ፤ 19በዛብሎን ወገን ላይ የአብድዩ ልጅ ሶማዒያስ፤ በንፍታሌም ወገን ላይ የዖዜሄል ልጅ ኢያሪሙት፤ 20በኤፍሬም ልጆች ላይ የአዛዝያ ልጅ ሆሴዕ፤ በምናሴ ነገድ እኩሌታ ላይ የፈዳያ ልጅ ኢዩኤል፤ 21በገለዓድ ምድር ባለው በምናሴ ነገድ እኩሌታ ላይ የዘብድያስ ልጅ ኢዮዳኢ፤ በብንያምም ልጆች ላይ የአበኔር ልጅ አሳሄል፤ 22በዳን ወገንም ላይ የኢዮራም ልጅ ዓዛርኤል፤ እነዚህ የእስራኤል ነገዶች አለቆች ነበሩ። 23ነገር ግን እግዚአብሔር ሕዝቡ እስራኤልን እንደ ሰማይ ከዋክብት ያበዛ ዘንድ ተናግሮ ነበርና ዳዊት ከሃያ ዓመት በታች የነበሩትን አልቈጠረም። 24የሶርህያ ልጅ ኢዮአብም መቍጠር ጀመረ፤ ነገር ግን አልፈጸመም፤ ስለዚህ ነገር በእስራኤል ላይ ቍጣ ሆነ፤ ቍጥራቸውም በንጉሡ በዳዊት የታሪክ መጽሐፍ አልተጻፈም።
25በንጉሡም ቤተ መዛግብት ላይ የዓዳኤል ልጅ ዓዝሞት ሹም ነበረ፤ በሜዳውም፥ በከተሞቹም፥ በመንደሮቹም፥ በግንቦቹም ቤተ መዛግብት ላይ የዖዝያ ልጅ ዮናታን ሹም ነበረ፤ 26መሬቱን በሚያበጃጁትና እርሻውን በሚያርሱት ላይ የክሉብ ልጅ ዔዝሪ ሹም ነበረ፤ 27በወይንም ቦታዎች ላይ ራማታዊው ሰሜኢ ሹም ነበረ፤ ለወይንም ጠጅ ዕቃ ቤት በሚሆነው በወይኑ ሰብል ላይ የሳፍኒው ዘብዲ ሹም ነበረ። 28በቈላውም ውስጥ ባሉት በወይራውና በሾላው ዛፎች ላይ ጌድራዊው በአልሐናን ሹም ነበረ፤ በዘይቱም ቤቶች ላይ ኢዮአስ ሹም ነበረ፤ 29በሳሮንም በሚሰማሩ ከብቶች ላይ ሳሮናዊው ሰጥራይ ሹም ነበረ፤ በሸለቆዎቹም ውስጥ በነበሩት ከብቶች ላይ የዓድላይ ልጅ ሳፋጥ ሹም ነበረ፤ 30በግመሎቹም ላይ እስማኤላዊው ኤቢያስ ሹም ነበረ፤ በአህዮቹም ላይ ሜሮኖታዊው ኢያድስ ሹም ነበረ፤ 31በበጎችም ላይ አጋራዊው ያዚዝ ሹም ነበረ። እነዚህ ሁሉ በንጉሡ በዳዊት ሀብት ላይ ሹሞች ነበሩ።
32አስተዋይና ጸሓፊ የነበረው በአባቱ በኩል የዳዊት አጎት ዮናታን አማካሪ ነበረ፤ የአክማኔም ልጅ ኢያሔኤል ከንጉሡ ልጆች ጋር ነበረ፤ 33አኪጦፌልም የንጉሡ አማካሪ ነበረ። አርካዊው ኩሲም የንጉሡ አንደኛ ወዳጅ ነበረ፤ 34ከአኪጦፌልም ቀጥሎ የበናያስ ልጅ ዮዳሔና አብያታር ነበሩ፤ ኢዮአብም የንጉሡ ሠራዊት አለቃ ነበረ።