መዝሙረ ዳዊት 64
64
1ለመዘምራን አለቃ፥ የዳዊት መዝሙር።
2አቤቱ፥ በሮሮዬ ድምፄን ስማ፥
ከጠላትም ፍርሃት ነፍሴን አድን።
3ከክፉዎች ደባ፥
ከዓመፀኞችም ብዛት ሰውረኝ።
4 #
መዝ. 11፥2፤ 37፥14፤ 55፥22፤ 57፥5። እንደ ሰይፍ ምላሳቸውን አሰሉ፥
እንደ ፍላጻ መራራ ነገርን ለመወርወር፥
5ንጹሕንም በስውር ለመንደፍ ቀስትን ገተሩ፥
ድንገት ይነድፉታል አይፈሩምም።
6ለእነርሱ ለራሳቸው ክፉ ነገርን አጸኑ፥
ወጥመድን ይሰውሩ ዘንድ ተማከሩ፥
ማንስ ያየናል? ይላሉ።
7 #
መዝ. 140፥3፤ ምሳ. 6፥14። ዓመፃን ፈለጓት፥
ሲፈትኑም አለቁ፥
የሰው የውስጥ አሳቡና ልቡ የጠለቀ ነው፥
8 #
መዝ. 7፥13-14፤ 38፥3፤ ዘዳ. 32፥42። እግዚአብሔርም ከፍ ከፍ ይላል።
ድንገተኛ ፍላጻም ያቈስላቸዋል፥
9 #
መዝ. 5፥11፤ 44፥14፤ 52፥6። አንደበታቸው ያሰናክላቸዋል፥
የሚያዩአቸውም ሁሉ ይደነግጣሉ።
10ሰዎች ሁሉ ፈሩ፥
የእግዚአብሔርንም ሥራ ተናገሩ፥
ሥራውንም አስተዋሉ።
11 #
መዝ. 36፥8፤ 57፥2። ጻድቅ በጌታ ደስ ይለዋል፥ በእርሱም ይታመናል፥
ልባቸውም ቅን የሆነ ሁሉ እልል ይላሉ።
Currently Selected:
መዝሙረ ዳዊት 64: መቅካእኤ
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
መዝሙረ ዳዊት 64
64
1ለመዘምራን አለቃ፥ የዳዊት መዝሙር።
2አቤቱ፥ በሮሮዬ ድምፄን ስማ፥
ከጠላትም ፍርሃት ነፍሴን አድን።
3ከክፉዎች ደባ፥
ከዓመፀኞችም ብዛት ሰውረኝ።
4 #
መዝ. 11፥2፤ 37፥14፤ 55፥22፤ 57፥5። እንደ ሰይፍ ምላሳቸውን አሰሉ፥
እንደ ፍላጻ መራራ ነገርን ለመወርወር፥
5ንጹሕንም በስውር ለመንደፍ ቀስትን ገተሩ፥
ድንገት ይነድፉታል አይፈሩምም።
6ለእነርሱ ለራሳቸው ክፉ ነገርን አጸኑ፥
ወጥመድን ይሰውሩ ዘንድ ተማከሩ፥
ማንስ ያየናል? ይላሉ።
7 #
መዝ. 140፥3፤ ምሳ. 6፥14። ዓመፃን ፈለጓት፥
ሲፈትኑም አለቁ፥
የሰው የውስጥ አሳቡና ልቡ የጠለቀ ነው፥
8 #
መዝ. 7፥13-14፤ 38፥3፤ ዘዳ. 32፥42። እግዚአብሔርም ከፍ ከፍ ይላል።
ድንገተኛ ፍላጻም ያቈስላቸዋል፥
9 #
መዝ. 5፥11፤ 44፥14፤ 52፥6። አንደበታቸው ያሰናክላቸዋል፥
የሚያዩአቸውም ሁሉ ይደነግጣሉ።
10ሰዎች ሁሉ ፈሩ፥
የእግዚአብሔርንም ሥራ ተናገሩ፥
ሥራውንም አስተዋሉ።
11 #
መዝ. 36፥8፤ 57፥2። ጻድቅ በጌታ ደስ ይለዋል፥ በእርሱም ይታመናል፥
ልባቸውም ቅን የሆነ ሁሉ እልል ይላሉ።