ትንቢተ ሚልክያስ መግቢያ

መግቢያ
ትንቢተ ሚልክያስ የተገኘው ከክርስቶስ ልደት በፊት በአምስተኛው ምእት ዓመት የኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ ዳግመኛ ከተሠራ በኋላ ነበር። ነቢዩ አጥብቆ የሚያሳስበው ካህናቱም ሆኑ ሕዝቡ ከእግዚአብሔር ጋር የገቡትን ቃል ኪዳን ማደስ እንዳለባቸው ነበር፤ የእግዚአብሔር ሕዝብ በአኗኗሩም ሆነ በአምልኮቱ መረን የተለቀቀና የተበላሸ እንደ ነበር ግልጥ ነው፤ ካህናቱና ሕዝቡ ተገቢውን መሥዋዕት ባለማቅረብና በሰጣቸውም መመሪያ ባለመኖር እግዚአብሔርን ለማታለል ይሞክሩ ነበር። ስለ ሆነም እግዚአብሔር መንገዱን ለማዘጋጀትና ቃል ኪዳኑን ለማወጅ መልእክተኛውን አስቀድሞ በመላክ በሕዝቡ ላይ ለመፍረድና ሕዝቡን ለማጥራት ይመጣል።
አጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት
1. ጌታ ለእስራኤል ሕዝብ ያለው ፍቅር (1፥1-5)
2. የእግዚአብሔር ፍርድ በካህናት ላይ (1፥6—2፥9)
2. የቃል ኪዳን መፍረስ (2፥10-17)
4. የጌታ መምጣት (3፥1-4)
5. እግዚአብሔርን ማታለል የማይገባ መሆኑ (3፥5-15)
6. የታማኞች መሸለምና የክፉዎች መቀጣት (3፥16—4፥6)

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ