በል እንግዲህ ና፤ ሕዝቤን፣ የእስራኤልን ልጆች ከግብጽ ምድር እንድታወጣቸው ወደ ፈርዖን እልክሃለሁ”። ሙሴ እግዚአብሔርን፣ “ወደ ፈርዖን የምሄድና የእስራኤልን ልጆች ከግብጽ የማወጣ እኔ ማን ነኝ?” አለው። እግዚአብሔርም፣ “እኔ ከአንተ ጋራ እሆናለሁ፤ እኔ የላክሁህ ለመሆኑ ምልክቱ ይህ ነው፤ ሕዝቡን ከግብጽ ካወጣሃቸው በኋላ በዚህ ተራራ ላይ እግዚአብሔርን ታመልካላችሁ” አለው። ሙሴም እግዚአብሔርን፣ “ወደ እስራኤል ልጆች ሄጄ፣ ‘የአባቶቻችሁ አምላክ ወደ እናንተ ልኮኛል’ ስላቸው ‘ስሙ ማን ነው?’ ብለው ቢጠይቁኝ ምን እላቸዋለሁ?” አለው። እግዚአብሔርም ሙሴን፣ “እኔ፣ ያለሁና የምኖር ነኝ፤ ስለዚህም ለእስራኤል ልጆች፣ ‘ያለና የሚኖር ልኮኛል’ ብለህ ንገራቸው” አለው።
ዘፀአት 3 ያንብቡ
ያዳምጡ ዘፀአት 3
ያጋሩ
ሁሉንም ሥሪቶች ያነጻጽሩ: ዘፀአት 3:10-14
5 ቀናት
እንደ ኢየሱስ ለመምራት ተጠርተናል። መሪነት የሚጀምረው በአንድ ሰው እንጂ በአቋም አይደለም፣ እና የመሪነት ግብ የእግዚአብሔርን ህዝብ ወደ አላማው ማንቀሳቀስ ነው። እያንዳንዱ እነዚህ ዕለታዊ ንባቦች በአመራር አውድ ውስጥ ጠንካራ መሰረት እንድትጥሉ ይረዱሃል፣ መሪ ከመሆንህ በፊት አገልጋይ እንደሆንክ እና አገልጋይ ከመሆንህ በፊት አንተ የእግዚአብሔር ተወዳጅ ልጅ እንደሆንክ ያስታውሰሃል።
ጥቅሶችን ያስቀምጡ፣ ያለበይነመረብ ያንብቡ፣ አጫጭር የትምህርት ቪዲዮዎችን ይመልከቱ እና ሌሎችም!
ቤት
መጽሐፍ ቅዱስ
እቅዶች
ቪዲዮዎች