1
የማቴዎስ ወንጌል 24:12-13
የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)
አማ2000
ከዐመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች። እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል።
සසඳන්න
የማቴዎስ ወንጌል 24:12-13 ගවේෂණය කරන්න
2
የማቴዎስ ወንጌል 24:14
ለአሕዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ የመንግሥት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል፤ በዚያን ጊዜም መጨረሻው ይመጣል።
የማቴዎስ ወንጌል 24:14 ගවේෂණය කරන්න
3
የማቴዎስ ወንጌል 24:6
ጦርንም የጦርንም ወሬ ትሰሙ ዘንድ አላችሁ፤ ይህ ሊሆን ግድ ነውና ተጠበቁ፥ አትደንግጡ፤ ዳሩ ግን መጨረሻው ገና ነው።
የማቴዎስ ወንጌል 24:6 ගවේෂණය කරන්න
4
የማቴዎስ ወንጌል 24:7-8
ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፤ ራብም ቸነፈርም የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል፤ እነዚህም ሁሉ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው።
የማቴዎስ ወንጌል 24:7-8 ගවේෂණය කරන්න
5
የማቴዎስ ወንጌል 24:35
ሰማይና ምድር ያልፋሉ፤ ቃሌ ግን አያልፍም።
የማቴዎስ ወንጌል 24:35 ගවේෂණය කරන්න
6
የማቴዎስ ወንጌል 24:5
ብዙዎች ‘እኔ ክርስቶስ ነኝ፤’ እያሉ በስሜ ይመጣሉና፤ ብዙዎችንም ያስታሉ።
የማቴዎስ ወንጌል 24:5 ගවේෂණය කරන්න
7
የማቴዎስ ወንጌል 24:9-11
“በዚያን ጊዜ ለመከራ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፤ ይገድሉአችሁማል፤ ስለ ስሜም በአሕዛብ ሁሉ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ። በዚያን ጊዜም ብዙዎች ይሰናከላሉ፤ እርስ በርሳቸውም አሳልፈው ይሰጣጣሉ፤ እርስ በርሳቸውም ይጣላሉ፤ ብዙ ሐሰተኞች ነቢያትም ይነሣሉ፤ ብዙዎችንም ያስታሉ፤
የማቴዎስ ወንጌል 24:9-11 ගවේෂණය කරන්න
8
የማቴዎስ ወንጌል 24:4
ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፤ “ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ።
የማቴዎስ ወንጌል 24:4 ගවේෂණය කරන්න
9
የማቴዎስ ወንጌል 24:44
ስለዚህ እናንተ ደግሞ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፤ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና።
የማቴዎስ ወንጌል 24:44 ගවේෂණය කරන්න
10
የማቴዎስ ወንጌል 24:42
ጌታችሁ በምን ሰዓት እንዲመጣ አታውቁምና እንግዲህ ንቁ።
የማቴዎስ ወንጌል 24:42 ගවේෂණය කරන්න
11
የማቴዎስ ወንጌል 24:36
“ስለዚያች ቀንና ስለዚያች ሰዓት ግን ከአባት ብቻ በቀር የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ ልጅም ቢሆን የሚያውቅ የለም።
የማቴዎስ ወንጌል 24:36 ගවේෂණය කරන්න
12
የማቴዎስ ወንጌል 24:24
ሐሰተኞች ክርስቶሶችና ሐሰተኞች ነቢያት ይነሣሉና፤ ቢቻላቸውስ የተመረጡትን እንኳ እስኪያስቱ ድረስ ታላላቅ ምልክትና ድንቅ ያሳያሉ።
የማቴዎስ ወንጌል 24:24 ගවේෂණය කරන්න
13
የማቴዎስ ወንጌል 24:37-39
የኖኅ ዘመን እንደ ነበረ የሰው ልጅ መምጣት እንዲሁ ይሆናልና። በዚያች ወራት ከጥፋት ውሃ በፊት፥ ኖኅ ወደ መርከብ እስከገባበት ቀን ድረስ፥ ሲበሉና ሲጠጡ ሲያገቡና ሲጋቡም እንደ ነበሩ፥ የጥፋት ውሃም መጥቶ ሁሉን እስከ ወሰደ ድረስ እንዳላወቁ፥ የሰው ልጅ መምጣት ደግሞ እንዲሁ ይሆናል።
የማቴዎስ ወንጌል 24:37-39 ගවේෂණය කරන්න
නිවස
බයිබලය
සැලසුම්
වීඩියෝ