1
ወደ ሮም ሰዎች 6:23
አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም
አማ05
ከኃጢአት የሚገኘው ዋጋ ሞት ነው፤ ከእግዚአብሔር የሚሰጠው ስጦታ ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት የሚገኘው የዘለዓለም ሕይወት ነው።
Compare
ወደ ሮም ሰዎች 6:23ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
2
ወደ ሮም ሰዎች 6:14
አሁን እናንተ የምትኖሩት ከጸጋ በታች እንጂ ከሕግ በታች ስላልሆነ ኃጢአት ሊገዛችሁ አይገባም።
ወደ ሮም ሰዎች 6:14ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
3
ወደ ሮም ሰዎች 6:4
በጥምቀት ከእርሱ ጋር በተቀበርን ጊዜ የእርሱም ሞት ተካፋዮች ሆነናል፤ ስለዚህ ክርስቶስ በአብ ክብር ከሞት እንደ ተነሣ እኛም በአዲስ ሕይወት እንኖራለን።
ወደ ሮም ሰዎች 6:4ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
4
ወደ ሮም ሰዎች 6:13
እንዲሁም የሰውነታችሁን ክፍሎች የዐመፅ መሣሪያ አድርጋችሁ ለኃጢአት አታስገዙ፤ ነገር ግን ከሞት ተነሥታችሁ ሕያዋን እንደ ሆናችሁ በማድረግ ራሳችሁን ለእግዚአብሔር አቅርቡ፤ የሰውነታችሁንም ክፍሎች ሁሉ የጽድቅ መሣሪያ አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር አስገዙ።
ወደ ሮም ሰዎች 6:13ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
5
ወደ ሮም ሰዎች 6:6
ኃጢአተኛው ሰውነታችን እንዲወገድና የኃጢአት ባሪያዎች መሆናችን እንዲቀር አሮጌው ሰውነታችን ከክርስቶስ ጋር መሰቀሉን እናውቃለን።
ወደ ሮም ሰዎች 6:6ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
6
ወደ ሮም ሰዎች 6:11
እንግዲህ እናንተ የመሞት ያኽል ከኃጢአት እንደ ተለያችሁና በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት ግን ለእግዚአብሔር በሕይወት እንደምትኖሩ አስቡ።
ወደ ሮም ሰዎች 6:11ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
7
ወደ ሮም ሰዎች 6:1-2
እንግዲህ ምን እንላለን? የእግዚአብሔር ጸጋ እንዲበዛ በኃጢአት ጸንተን እንኑርን? አይደለም! እኛ በሞት የመለየትን ያኽል ከኃጢአት የተለየን ሆነን ሳለ እንዴት በኃጢአት ጸንተን እንኖራለን?
ወደ ሮም ሰዎች 6:1-2ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
8
ወደ ሮም ሰዎች 6:16
ለአንድ ሰው አገልጋዮች ሆናችሁ ለመታዘዝ ራሳችሁን ስታቀርቡ ለዚያ ለምትታዘዙለት ሰው አገልጋዮች መሆናችሁን ታውቃላችሁ፤ እንዲሁም ለኃጢአት ብትታዘዙ ሞትን ለሚያመጣባችሁ ኃጢአት አገልጋዮች ትሆናላችሁ፤ ለእግዚአብሔር ብትታዘዙ ግን ጽድቅን ታገኛላችሁ።
ወደ ሮም ሰዎች 6:16ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
9
ወደ ሮም ሰዎች 6:17-18
እናንተ አስቀድሞ የኃጢአት ባሪያዎች ነበራችሁ፤ አሁን ግን ለተቀበላችሁት ትምህርት ከልብ በመታዘዛችሁ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን። ከኃጢአት ባርነት ነጻ ወጥታችሁ የጽድቅ አገልጋዮች ሆናችኋል።
ወደ ሮም ሰዎች 6:17-18ਪੜਚੋਲ ਕਰੋ
Home
ਬਾਈਬਲ
Plans
ਵੀਡੀਓ