1
የሉቃስ ወንጌል 9:23
አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም
አማ05
ለሁሉም ደግሞ እንዲህ አላቸው፦ “ሊከተለኝ የሚወድ ቢኖር ራሱን ይካድ፤ በየቀኑም መስቀሉን ተሸክሞ ይከተለኝ፤
နှိုင်းယှဉ်
የሉቃስ ወንጌል 9:23ရှာဖွေလေ့လာလိုက်ပါ။
2
የሉቃስ ወንጌል 9:24
ከእኔ ይልቅ ለሕይወቱ የሚሳሳ ሁሉ ያጠፋታል፤ ስለ እኔ ሕይወቱን አሳልፎ የሚሰጥ ግን ያድናታል።
የሉቃስ ወንጌል 9:24ရှာဖွေလေ့လာလိုက်ပါ။
3
የሉቃስ ወንጌል 9:62
ኢየሱስም “ለማረስ በእጁ ዕርፍ ይዞ ወደ ኋላ የሚመለከት ሰው ለእግዚአብሔር መንግሥት የተገባ አይደለም፤” ሲል መለሰለት።
የሉቃስ ወንጌል 9:62ရှာဖွေလေ့လာလိုက်ပါ။
4
የሉቃስ ወንጌል 9:25
ሰው የዓለምን ሀብት ሁሉ ቢያገኝ፥ ነፍሱን ግን ቢያጠፋ ምን ይጠቅመዋል?
የሉቃስ ወንጌል 9:25ရှာဖွေလေ့လာလိုက်ပါ။
5
የሉቃስ ወንጌል 9:26
በእኔና በቃሌ የሚያፍር ሁሉ የሰው ልጅም በራሱ ክብርና በአባቱ ክብር፥ እንዲሁም በቅዱሳን መላእክቱ ክብር በሚመጣበት ጊዜ በእርሱ ያፍርበታል።
የሉቃስ ወንጌል 9:26ရှာဖွေလေ့လာလိုက်ပါ။
6
የሉቃስ ወንጌል 9:58
ኢየሱስም “ቀበሮዎች ጒድጓድ አላቸው፤ የሰማይ ወፎችም ጎጆ አላቸው፤ የሰው ልጅ ግን ራሱን እንኳ አስጠግቶ የሚያሳርፍበት ስፍራ የለውም፤” ሲል መለሰለት።
የሉቃስ ወንጌል 9:58ရှာဖွေလေ့လာလိုက်ပါ။
7
የሉቃስ ወንጌል 9:48
እርሱም “ይህን ሕፃን በስሜ የሚቀበል ሁሉ እኔን ይቀበላል፤ እኔንም የሚቀበል ሁሉ የላከኝን ይቀበላል። ከእናንተ መካከል ከሁላችሁም የሚያንስ እርሱ ከሁሉ የሚበልጥ ይሆናል፤” አላቸው።
የሉቃስ ወንጌል 9:48ရှာဖွေလေ့လာလိုက်ပါ။
ပင်မစာမျက်နှာ
သမ္မာကျမ်းစာ
အစီအစဉ်များ
ဗီဒီယိုများ