1
የዮሐንስ ወንጌል 12:26
አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም
አማ05
እኔን ማገልገል የሚፈልግ ይከተለኝ፤ እኔ ባለሁበት አገልጋዬ በዚያ ይሆናል፤ የሚያገለግለኝንም አብ ያከብረዋል።”
နှိုင်းယှဉ်
የዮሐንስ ወንጌል 12:26ရှာဖွေလေ့လာလိုက်ပါ။
2
የዮሐንስ ወንጌል 12:25
ሕይወቱን የሚወድ ያጠፋታል፤ በዚህ ዓለም ሕይወቱን የሚጠላ ግን ለዘለዓለም ሕይወት ይጠብቃታል።
የዮሐንስ ወንጌል 12:25ရှာဖွေလေ့လာလိုက်ပါ။
3
የዮሐንስ ወንጌል 12:24
እውነት፥ እውነት እላችኋለሁ፤ የስንዴ ቅንጣት በመሬት ወድቃ ካልሞተች፥ ብቻዋን ትቀራለች፤ ከሞተች ግን ብዙ ታፈራለች።
የዮሐንስ ወንጌል 12:24ရှာဖွေလေ့လာလိုက်ပါ။
4
የዮሐንስ ወንጌል 12:46
በእኔ የሚያምን ሁሉ በጨለማ እንዳይኖር እኔ ብርሃን ሆኜ ወደ ዓለም መጥቻለሁ።
የዮሐንስ ወንጌል 12:46ရှာဖွေလေ့လာလိုက်ပါ။
5
የዮሐንስ ወንጌል 12:47
ቃሌን ሰምቶ በሥራ ላይ የማያውለውን የምፈርድበት እኔ አይደለሁም፤ እኔ የመጣሁት ዓለምን ለማዳን ነው እንጂ በዓለም ላይ ለመፍረድ አይደለም።
የዮሐንስ ወንጌል 12:47ရှာဖွေလေ့လာလိုက်ပါ။
6
የዮሐንስ ወንጌል 12:3
በዚያን ጊዜ ማርያም ዋጋው እጅግ የከበረ ከንጹሕ ናርዶስ የተሠራ፥ ግማሽ ሊትር የሚሆን አንድ ብልቃጥ ሽቶ ወስዳ፥ የኢየሱስን እግሮች ቀባች፤ በጠጒርዋም አበሰቻቸው፤ ቤቱም በሽቶው መዓዛ ተሞላ።
የዮሐንስ ወንጌል 12:3ရှာဖွေလေ့လာလိုက်ပါ။
7
የዮሐንስ ወንጌል 12:13
ስለዚህ የዘንባባ ቅርንጫፍ ይዘው ሊቀበሉት ወጡ፤ “ሆሳዕና! በጌታ ስም የሚመጣ የእስራኤል ንጉሥ የተባረከ ነው!” እያሉ ይጮኹ ነበር።
የዮሐንስ ወንጌል 12:13ရှာဖွေလေ့လာလိုက်ပါ။
8
የዮሐንስ ወንጌል 12:23
ኢየሱስም እንዲህ ሲል መለሰላቸው፦ “እነሆ፥ የሰው ልጅ የሚከበርበት ሰዓት ደርሶአል፤
የዮሐንስ ወንጌል 12:23ရှာဖွေလေ့လာလိုက်ပါ။
ပင်မစာမျက်နှာ
သမ္မာကျမ်းစာ
အစီအစဉ်များ
ဗီဒီယိုများ