1
የማርቆስ ወንጌል 16:15
አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም
አማ05
እንዲህም አላቸው፦ “ወደ መላው ዓለም ሂዱ፤ ለሰው ሁሉ ወንጌልን አስተምሩ።
Bera saman
Njòttu የማርቆስ ወንጌል 16:15
2
የማርቆስ ወንጌል 16:17-18
በእኔ የሚያምኑ ሁሉ እነዚህን ተአምራት ያደርጋሉ፤ በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ፤ በአዲስ ቋንቋም ይናገራሉ፤ እባቦችን ቢይዙ፥ ወይም የሚገድል መርዝ እንኳ ቢጠጡ አይጐዳቸውም፤ እጃቸውን በበሽተኞች ላይ ሲጭኑ በሽተኞቹ ይድናሉ።”
Njòttu የማርቆስ ወንጌል 16:17-18
3
የማርቆስ ወንጌል 16:16
ያመነና የተጠመቀ ይድናል፤ የማያምን ግን ይፈረድበታል።
Njòttu የማርቆስ ወንጌል 16:16
4
የማርቆስ ወንጌል 16:20
ደቀ መዛሙርቱም በየስፍራው ሁሉ እየሄዱ አስተማሩ፤ ጌታም ከእነርሱ ጋር ይሠራ ነበር። ተአምራትንም የማድረግ ሥልጣን በመስጠት የትምህርታቸውን እውነተኛነት ያጸና ነበር።]
Njòttu የማርቆስ ወንጌል 16:20
5
የማርቆስ ወንጌል 16:6
እርሱ ግን እንዲህ አላቸው፦ “አይዞአችሁ፥ አትደንግጡ፤ እናንተ የምትፈልጉት ተሰቅሎ የነበረውን የናዝሬቱን ኢየሱስን እንደ ሆነ ዐውቃለሁ፤ እርሱ ተነሥቶአል፤ እዚህ የለም፤ የተቀበረበትም ቦታ ይኸውላችሁ፤ ተመልከቱ።
Njòttu የማርቆስ ወንጌል 16:6
6
የማርቆስ ወንጌል 16:4-5
ይህንንም ያሉት መቃብሩ የተዘጋበት ድንጋይ እጅግ ትልቅ ስለ ነበረ ነው፤ ቀና ብለውም በተመለከቱ ጊዜ ግን ድንጋዩ ወደ ጐን ተንከባሎ አዩት። ወደ መቃብሩም በገቡ ጊዜ ነጭ ልብስ የለበሰ ጐልማሳ በስተቀኝ በኩል ተቀምጦ በማየታቸው ደነገጡ።
Njòttu የማርቆስ ወንጌል 16:4-5
Heim
Biblía
Áætlanir
Myndbönd