1
ኦሪት ዘፍጥረት 13:15
የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)
አማ2000
የምታያትን ምድር ሁሉ ለአንተና ለዘርህ ለዘለዓለም እሰጣለሁና።
השווה
חקרו ኦሪት ዘፍጥረት 13:15
2
ኦሪት ዘፍጥረት 13:14
ሎጥ ከተለየው በኋላም እግዚአብሔር አብራምን አለው፥ “ዐይንህን አንሣና አንተ ካለህበት ስፍራ ወደ መስዕና ወደ አዜብ፥ ወደ ምሥራቅና ወደ ምዕራብ እይ፤
חקרו ኦሪት ዘፍጥረት 13:14
3
ኦሪት ዘፍጥረት 13:16
ዘርህንም እንደ ባሕር አሸዋ አደርጋለሁ፤ የባሕር አሸዋን ይቈጥር ዘንድ የሚችል ሰው ቢኖር ዘርህ ደግሞ ይቈጠራል።
חקרו ኦሪት ዘፍጥረት 13:16
4
ኦሪት ዘፍጥረት 13:8
አብራምም ሎጥን አለው፥ “እኛ ወንድማማች ነንና በእኔና በአንተ፥ በእረኞቼና በእረኞችህ መካከል ጠብ አይሁን።
חקרו ኦሪት ዘፍጥረት 13:8
5
ኦሪት ዘፍጥረት 13:18
አብራምም ድንኳኑን ነቀለ፤ መጥቶም በኬብሮን ባለው የመምሬ ዛፍ ተቀመጠ፤ በዚያም ለእግዚአብሔር መሠውያን ሠራ።
חקרו ኦሪት ዘፍጥረት 13:18
6
ኦሪት ዘፍጥረት 13:10
ሎጥም ዓይኖቹን አነሣ፤ በዮርዳኖስ ዙሪያ ያለውንም ሀገር ሁሉ ውኃ የሞላበት መሆኑን አየ፤ እግዚአብሔር ሰዶምንና ገሞራን ከማጥፋቱ አስቀድሞ እስከ ሴጎር ድረስ እንደ እግዚአብሔር ገነትና እንደ ግብፅ ምድር እንደ ነበረ አየ።
חקרו ኦሪት ዘፍጥረት 13:10
בית
כתבי הקודש
תכניות
קטעי וידאו