1
ኦሪት ዘፍጥረት 9:12-13
አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም
አማ05
እግዚአብሔርም እንዲህ አለ፦ “ከእናንተና ከሕያዋን ፍጥረቶች ሁሉ ጋር ለምገባው ለዚህ ለዘለዓለማዊ ቃል ኪዳን ምልክት ይሆን ዘንድ፥ ቀስቴን በደመናዎች ላይ አደርጋለሁ፤ ይህም ቀስት ከምድር ጋር ለገባሁት ቃል ኪዳን ምልክት ሆኖ ይኖራል።
השווה
חקרו ኦሪት ዘፍጥረት 9:12-13
2
ኦሪት ዘፍጥረት 9:16
ቀስት በደመናዎች ላይ በሚታይበት ጊዜ ተመልክቼ በእኔና በምድር ላይ ባሉት ሕይወት ባላቸው ፍጥረቶች መካከል ያለውን ዘለዓለማዊ ቃል ኪዳን አስታውሳለሁ።”
חקרו ኦሪት ዘፍጥረት 9:16
3
ኦሪት ዘፍጥረት 9:6
ሰው የተፈጠረው በእግዚአብሔር አምሳያ ስለ ሆነ፥ ሰውን የሚገድል ሁሉ በሰው እጅ ይሞታል።
חקרו ኦሪት ዘፍጥረት 9:6
4
ኦሪት ዘፍጥረት 9:1
እግዚአብሔር ኖኅንና ልጆቹን ባረካቸው፤ እንዲህም አላቸው፤ “ብዙ፥ ተባዙ ምድርንም ሙሉአት፤
חקרו ኦሪት ዘፍጥረት 9:1
5
ኦሪት ዘፍጥረት 9:3
ከዚህ በፊት የአትክልት ዐይነቶችን ምግብ አድርጌ እንደሰጠኋችሁ እነዚህንም ተንቀሳቃሽ ፍጥረቶች ሁሉ ምግብ እንዲሆኑአችሁ ሰጥቻችኋለሁ።
חקרו ኦሪት ዘፍጥረት 9:3
6
ኦሪት ዘፍጥረት 9:2
እንስሶች፥ ወፎች፥ በደረታቸው እየተሳቡ የሚንቀሳቀሱ ፍጥረቶችና ዓሣዎች ሁሉ እናንተን በመፍራትና በመደንገጥ ይኑሩ፤ ሁሉም በሥልጣናችሁ ሥር ይሁኑ።
חקרו ኦሪት ዘፍጥረት 9:2
7
ኦሪት ዘፍጥረት 9:7
“እናንተ ፍሬያማ ሆናችሁ ተባዙ፤ ዘራችሁ በምድር ላይ ይብዛ።”
חקרו ኦሪት ዘፍጥረት 9:7
בית
כתבי הקודש
תכניות
קטעי וידאו