1
ወደ ገላትያ ሰዎች 5:22-23
መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)
መቅካእኤ
የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው። እንደ እነዚህ ያሉትን የሚቃረን ሕግ የለም።
Compare
Avasta ወደ ገላትያ ሰዎች 5:22-23
2
ወደ ገላትያ ሰዎች 5:16
ይህን እላለሁ፥ በመንፈስ ተመላለሱ፥ የሥጋንም ምኞት አትፈጽሙ።
Avasta ወደ ገላትያ ሰዎች 5:16
3
ወደ ገላትያ ሰዎች 5:25
በመንፈስ የምንኖር ከሆንን በመንፈስ ደግሞ እንመላለስ።
Avasta ወደ ገላትያ ሰዎች 5:25
4
ወደ ገላትያ ሰዎች 5:24
የክርስቶስ ኢየሱስ የሆኑት ሥጋን ከመሻቱና ከምኞቱ ጋር ሰቅለውታል።
Avasta ወደ ገላትያ ሰዎች 5:24
5
ወደ ገላትያ ሰዎች 5:19-21
የሥጋ ሥራም ግልጽ ነው፤ እርሱም ዝሙት፥ ርኩሰት፥ መዳራት፥ ጣዖትን ማምለክ፥ አስማት፥ ጠላትነት፥ ጠብ፥ ቅናት፥ ቁጣ፥ አድመኛነት፥ መለያየት፥ መናፍቅነት፥ ምቀኝነት፥ መግደል፥ ስካር፥ መሶልሶል፥ ይህንም የሚመስል ነው። አስቀድሜ እንደ ነገርኋችሁ፥ አስቀድሜም እንዳልሁ፥ እንደዚህ ያሉትን የሚያደርጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም።
Avasta ወደ ገላትያ ሰዎች 5:19-21
6
ወደ ገላትያ ሰዎች 5:13
ወንድሞች ሆይ! እናንተ ለነጻነት ተጠርታችኋል፤ ነጻነታችሁ ለሥጋ ብቻ ምክንያት አይስጥ፤ ነገር ግን በፍቅር አንዳችሁ ለሌላችሁ ባርያዎች ሁኑ።
Avasta ወደ ገላትያ ሰዎች 5:13
7
ወደ ገላትያ ሰዎች 5:17
ሥጋ መንፈስ የማይፈልገውን ይመኛል፥ መንፈስም ሥጋ የማይፈልገውን፤ እነዚህ እርስ በርሳቸው ስለሚቀዋወሙ የምትፈልጉትን ማድረግ አትችሉም።
Avasta ወደ ገላትያ ሰዎች 5:17
8
ወደ ገላትያ ሰዎች 5:14
ሕግ ሁሉ በአንድ ቃል ተፈጽሟል፥ እርሱም “ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ” የሚል ነው።
Avasta ወደ ገላትያ ሰዎች 5:14
9
ወደ ገላትያ ሰዎች 5:26
እርስ በርሳችን እየተተነኳኮስንና እርስ በርሳችን እየተቀናናን በከንቱ አንመካ።
Avasta ወደ ገላትያ ሰዎች 5:26
10
ወደ ገላትያ ሰዎች 5:1
በነጻነት እንድንኖር ክርስቶስ ነጻ አወጣን፤ እንግዲህ ጸንታችሁ ቁሙ፤ በባርነት ቀንበር እንደገና አትያዙ።
Avasta ወደ ገላትያ ሰዎች 5:1
Home
Bible
Plans
Videod