1
ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:1-2
መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)
መቅካእኤ
እንግዲህ እንደ ተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን ምሰሉ፤ ክርስቶስም እንዳፈቀራችሁ፥ ስለ እናንተም ለእግዚአብሔር መልካም መዓዛ ያለው መባንና መሥዋዕት አድርጎ ራሱን አሳልፎ እንደሰጠ፥ በፍቅር ተመላለሱ።
Compare
Avasta ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:1-2
2
ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:15-16
እንግዲህ ስለ አኗኗሯችሁ በጥንቃቄ ተጠበቁ፥ እንደ ጥበበኞች እንጂ ጥበብ እንደሌላቸው አይሁን፤ ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን በሚገባ ዋጁ።
Avasta ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:15-16
3
ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:18-20
መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ ብክነት እንደ ሆነው በወይን ጠጅ አትስከሩ፤ በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤ ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ፤ ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ።
Avasta ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:18-20
4
ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:17
ስለዚህ የጌታ ፈቃድ ምን እንደሆነ አስተውሉ እንጂ ሞኞች አትሁኑ።
Avasta ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:17
5
ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:25
ባሎች ሆይ! ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ወደዳትና ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ እንደሰጣት፥ ሚስቶቻችሁን ውደዱ፤
Avasta ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:25
6
ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:8
ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁ፤ አሁን ግን በጌታ ብርሃን ናችሁ፤ እንደ ብርሃን ልጆች ተመላለሱ፤
Avasta ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:8
7
ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:21
እያንዳንዳችሁ በክርስቶስ ፍርሃት የተገዛችሁ ሁኑ።
Avasta ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:21
8
ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:22
ሚስቶች ሆይ! ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁ ተገዙ፤
Avasta ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:22
9
ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:33
ሆኖም ከእናንተ እያንዳንዱ የገዛ ሚስቱን እንደ ራሱ አድርጎ ይውደዳት፤ ሚስትም ባልዋን ታክብር።
Avasta ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:33
10
ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:31
“ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፤ ከሚስቱም ጋር ይተባበራል፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ።”
Avasta ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:31
11
ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:11
ፍሬም ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር አትተባበሩ፤ ይልቁን ግለጡት፤
Avasta ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:11
Home
Bible
Plans
Videod